Site icon ETHIO12.COM

በባኮ ቲቤ ወረዳ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ3 ሰዎች ህይወት አለፈ

በምዕራብ ሸዋ ዞን ባኮ ቲቤ ወረዳ ሾቦካ ከተማ አቅራቢያ በተከሰተ የትራፊክ አደጋ የሶስት ሰዎች ህይወት አለፈ፡፡

አደጋው ሁለት ከባድ ተሽከርካሪዎች እርስ በርስ በፈጠሩት ግጭት የተከሰተ ነው።

በተከሰተው አደጋ የሶስት ሰዎች ህይወት ሲያልፍ÷ግጭቱን ተከትሎ በተፈጠረው የእሳት ቃጠሎም ንብረት ላይ ጉዳት መድረሱ ተመላክቷል፡፡

የአካባቢው ማህበረሰብ ባደረገው ርብርብ የተነሳው እሳት በቁጥጥር ስር መዋሉ እና የትራንስፖር አገልግሎት መቀጠሉም ተገልጿል፡፡ via OMN

Exit mobile version