Site icon ETHIO12.COM

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እጣ ወጥቶባቸው የነበሩ ኮንደሚኒየም ቤቶች ቁልፍ ለባለ ዕድለኞ አስረከበ

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እጣ ወጥቶባቸው የነበሩ የ20/80 እና የ40/60 ኮንደሚኒየም ቤቶች ቁልፍን ለባለ ዕድለኞ አስረከበ

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በቤቶች ልማት ፕሮግራም ተገንብተው እጣ የወጣባቸውን የ20/80 እና የ40/60 መኖሪያ ኮንደሚኒየም ቤቶች ቁልፍን ለባለ ዕድለኞች አስረከበ።

የ20/80 ኮንደሚኒየም ቤቶች ተገንብተው ለባለዕድለኞች ሲተላለፉ ይህ ለ13ኛ ጊዜ ሲሆን የ40/60 ኮንደሚኒየም ቤቶች ግንባታ ርክክብ ሥነ-ሥርዓት የተፈጸመው ደግሞ ለ2ኛ ጊዜ መሆኑን የከተማ አስተዳደሩ አመልክቷል፡፡

ርክክብ የተፈጸመባቸው ቤቶች “ቱሪስት ሳይት” ተብሎ በሚጠራው አካባቢ የተገነቡት እንደሆኑም ተጠቅሷል።

Exit mobile version