Site icon ETHIO12.COM

ዩክሬን የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ተማሪዎች ወደ ፖላንድ ጉዞ መጀመራቸው ተገለፀ

ለአራተኛ ቀን ጦርነት በቀጠለባት ዩክሬን የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ተማሪዎች ወደ ፖላንድ ጉዞ መጀመራቸውን በጀርመን የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ በቅርቡ ለቢቢሲ ገልጿል.
ኢትዮጵያውን ተማሪዎች ወደ ፓላንድ እንዲሻገሩ ከፖላንድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መግባባት ላይ መደረሱን ተከትሎ ጉዞ የጀመሩ መሆኑንም ቢቢሲ መረዳት ችሏል።
የሩሲያ ኃይሎች ወደ ዋና መዲናዋ ኪዬቭ መግባታቸው እየተነገረ ካለችው ዩክሬን ወደ ፖላንድ ለመውጣት በሚደረገው ሙከራ ከፍተኛ የሆነ የትራፊክና የመኪና መጨናነቅ መኖሩም ተገልጿል
በተለይም ወደ ፖላንድ ድንበር አካባቢ የሚገኙ ተማሪዎች እንቅስቃሴ የጀመሩ ሲሆን ሆኖም አንዳንድ በተዘጉ ስፍራዎች ላይ ያሉ ተማሪዎች መረጋጋት እስከሚፈጠር ድረስ የተወሰነ ጊዜ ሊቆዩ ይችላሉ ተብሏል።
.
via- @BBC New Amharic

Photo- African students at the Ukraine and Poland border

Exit mobile version