– 240 ሺህ ሚደርሱ የከፍተኛ ትምህርት ተመራቂዎች የመውጫ ፈተና ይወስዳሉ
በሚቀጥሉት ሁለት ወራት በአገር አቀፍ ደረጃ የትምህርት ቤቶችን ደረጃ ለማሻሻል የሚያስችል ንቅናቄ ሊካሄድ መሆኑን የትምህርት ሚኒስትር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ገለጹ።
ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የትምህርት ሚኒስቴርን የ2015 ዓ.ም የዘጠኝ ወራት የስራ አፈፃፀም ሪፖርት ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አቅርበዋል።
በሪፖርታቸው ትምህርት ቤቶችን በማሻሻል የመማር ማስተማር ሒደቱ ላይ የሚታዩ ክፍተቶችን የማስተካከል ስራዎች ይከናወናሉ ብለዋል።
በመሆኑም በሚቀጥሉት ሁለት ወራት የትምህርት ቤቶችን ደረጃ ለማሻሻል የሚያስችል የሁሉንም ባለድርሻ አካላት ትብብር የሚጠይቅ አገራዊ የሕዝብ ንቅናቄ የሚደረግ መሆኑን ገልፀዋል።
በሀገር አቀፍ ደረጃ 47 ሺህ አጠቃላይ ትምህርት የሚሰጡ የትምህርት ተቋማት መኖራቸውን ጠቅሰው ያሉበትን ደረጃ በሚመለከት ቀደም ብሎ ጥናት መደረጉን ተናግረዋል።
በዚህም በርካታ ትምህርት ቤቶች የሚጠበቀውን ደረጃ የማያሟሉ መሆናቸው ተረጋግጧል ያሉት ሚኒስትሩ በተባበረ አቅም የትምህርት ቤቶቹን ደረጃ ማሻሻል ያስፈልጋል ሲል ኢዜአ ዘግቧል።
የትምህርት ቤቶችን መሰረተ ልማት ለማሟላት ሕብረተሰቡን በማስተባበር በተሰበሰው 11 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር 8 ሺህ 702 ትምህርት ቤቶች ተጠግነው አገልግሎት እንዲሰጡ መደረጉን ገልጸዋል።
ዘንድሮ 240 ሺህ ሚደርሱ የከፍተኛ ትምህርት ተመራቂዎች የመውጫ ፈተና ይወስዳሉ ፡- ትምህርት ሚኒስቴር
240 ሺህ ለሚደርሱ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች በበይነ-መረብ የመውጫ ፈተና ለመሥጠት መዘጋጀቱን ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡
የትምህርት ሚኒስትሩ ኘሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እንደገለጹት ÷ በ2015 ዓ.ም በመጀመሪያ ዲግሪ ኘሮግራም ለሚመረቁ ተማሪዎች የመውጫ ፈተና ለመሥጠት ብሉ -ኘሪንት ተዘጋጅቷል፡፡
የመውጫ ፈተና የክፍያ ተመን ረቂቅ መመሪያ መዘጋጀቱንም ለምክር ቤቱ ባቀረቡት ሪፖርት አብራርተዋል፡፡
የመውጫ ፈተና ስትራቴጂ ማስፈፀሚያ መመሪያ እና የድርጊት መርሐ-ግብር ዝግጅት መጠናቀቁንም ጠቁመዋል፡፡
በመውጫ ፈተና የሚካተቱ የትምህርት ዓይነቶች ተለይተው በቅድመ-ምረቃ በሚሰጡ በሁሉም የትምህርት መስኮች የፈተና ንድፍ ማሳያ መዘጋጀቱን ማስረዳታቸውን ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡
OBN
- Ethiopia Working To Secure New Development Bank MembershipThe Ministry of Foreign Affairs disclosed that Ethiopia is working hard to become member of BRICS’ New Development Bank. In a media briefing regarding the country’s diplomatic activities over the week, Spokesperson of the Ministry… Read more: Ethiopia Working To Secure New Development Bank Membership
- የትግራይ ክልል ታጣቂዎች ዳግም ዝርፊያ እያፈጸሙ ነው፤ የተማሪዎች መጽሃፍትን “የአማራ ክልል ናቸው እየሉ ቀደዋል”በአላማጣ ከተማ በተለየ መልኩ የትግራይ ክልል ታጣቂዎች በከተማዋ ውስጥ እንደሚንቀሳቀሱ ነዋሪዎች መመስከራቸውን ቢቢሲ አስታወቀ። ይህ የተገለጸው ከአለማጣ እና አካባቢው የተፈናቀሉ ሰዎች ቁጥር ከሃምሳ ሺህ በላይ ማሻቀቡ ይፋ እየሆነ ባለበት ወቅት ነው። መንግስት ሰላማዊ ዜጎችን ማህበራዊ… Read more: የትግራይ ክልል ታጣቂዎች ዳግም ዝርፊያ እያፈጸሙ ነው፤ የተማሪዎች መጽሃፍትን “የአማራ ክልል ናቸው እየሉ ቀደዋል”
- በዘንድሮው ዓመት የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ኢትዮጵያ ሰባት ነጥብ ሁለት ቢሊዮን ችግኝ ልትተክል ነውለዘንድሮ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር 6 ነጥብ 5 ቢሊየን ችግኝ ለመትከል ዕቅድ መያዙንna ለዚህም ተግባራዊነት ከሰባት ነጥብ ሁለት ቢሊየን በላይ ችግኝ መዘጋጀቱን ተገለጸ። 1 ነጥብ 2 ሚሊየን ሄክታር መሬት ለተከላ ተዘጋጅቷል። ለዘንድሮው ዓመት የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር… Read more: በዘንድሮው ዓመት የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ኢትዮጵያ ሰባት ነጥብ ሁለት ቢሊዮን ችግኝ ልትተክል ነው
- አፍሪካ ህብረት ” የውጭ ምንዛሪ ሒሳቡን ወደ ሌላ ሀገር ሊያዘዋውር ነው” የሚለው ዜና ሃሰት መሆኑን አረጋግጠአፍሪካ ህብረት የውጭ ምንዛሬ አካውንቱን ወደ ሌላ አገር እንደሚያዘዋውር ተጠቅሶ በህብረቱ ስም የወጣው ዜና ሃሰት፣ ሆን ተብሎ የተቀነባበረ መሆኑን መንግስት አስታወቀ። መረጃው ቀድሞውንም ዜናው “ሴራ” ነው በሚል አስተያየት ከሰጡ ወገኖች ጋር የሚስማማ ሆኗል። ቀሲስ በላይ… Read more: አፍሪካ ህብረት ” የውጭ ምንዛሪ ሒሳቡን ወደ ሌላ ሀገር ሊያዘዋውር ነው” የሚለው ዜና ሃሰት መሆኑን አረጋግጠ
- አፍሪቃ ህብረት ምን አሰጋውና “ገንዘቤን ወደ ሌላ አገር ለማዛወር እያሰብኩ ነው” ሲል ተንሿከከ፤ የጾምና የፍስክ ዜናዎችባንኩ የክፍያ ሰነድ ቀረበለት። ማጣሪያ ጥያቄ ለህብረቱ አቀረበ። ሃሰት ሆኖ ተገኘና ፖሊስ ተጠርጣሪዎቹን ያዘ። ጉዳዩ ወደ ህግ አመራ። አሁን ምኑ ነው አፍሪካ ህብረትን ስጋት ላይ ጥሎት አካውንቱን ወደ ሌላ አገር እንዲወስድ ያስገደደው? ከሆነም ህብረቱ ይህን… Read more: አፍሪቃ ህብረት ምን አሰጋውና “ገንዘቤን ወደ ሌላ አገር ለማዛወር እያሰብኩ ነው” ሲል ተንሿከከ፤ የጾምና የፍስክ ዜናዎች