ስድስተኛው አገራዊው ምርጫ በሰላም እንዲጠናቀቅ አስፈለጊው ዝግጅት መደረጉ ተጠቆመ ፣”ምርጫውን ለማደናቀፍ፣ የግድቡን ሙሌት ለማስተጓጎል የሚንቀሳቀሱ አሉ፤ ከእይታችን ውጭ ግን አይደሉም” ትብሏል። ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አሕመድ ሕዝብ ወትቶ ያለ ስጋት እንዲመርጥ ጥሪ አቅርበዋል። የፓርቲዎች ሕብረት ምርጫው በሰላማዊ መነግድ እንዲጠናቀቅ አስፈላጊውን ሁሉ እንደሚያደርግ ማስታወቁ አይዘነጋም።
የፌዴራል፣ የክልል የደህንነትና የፀጥታ መዋቅሮች በቂ ዝግጅት ማድረጋቸውን ያስታወቁት የብሔራዊ ደህንነትና መረጃ አገልግሎት ዳይሬክተር ጀነራል አቶ ተመስገን ጥሩነህ ናቸው። የፌዴራል፣ የክልል የደህንነትና የፀጥታ አካላት ግብረኅይል ወቅታዊ የሀገሪቷን ደህንነት የሚገመግም እና ቀጣይ አቅጣጫዎችን የሚያስቀምጥ ውይይት እያደረጉ መሆኑም ታውቋል።
በዚሁ ወቅት የብሔራዊ ደህንነት እና መረጃ አገልግሎት ዳይሬክተር ጀነራል አቶ ተመስገን ጥሩነህ ቀጣዩ የምርጫ እና ድህረ ምርጫ ሰላማዊ እንዲሆን በቂ ዝግጅት እንደተደረገ መናገራቸውን የኢቢሲ ዘግባ አመልክቷል። ምርጫውንና ለማደናቀፍና የግድቡን ሙሌት ለማስተጓጎል የሚሰሩ የውጭ እና የውስጥ ጠላቶች መኖራቸውን የተናገሩት አቶ ተመስገን ሁሉም አይነት እንቅስቃሴ ከደህንነቱ መስሪያ ቤት ክትትል የሚያመልጥ እንዳልሆነ አመልከዋል። ይህንኑ አተናክሮ በአስተማማኝ ለመከወን የፌዴራል፣ የክልል የፀጥታና ደህንነት አካላት የጋራ ግብረ ሀይልም የሀገሪቷን ወቅታዊ የደህንነት ሁኔታ በመገምገም ቀጣይ አቅጣጫዎችን ያስቀምጣሉ ተብሎ ይጠበቃል።
በተመሳሳይ የምርጫ ዜና ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ምርጫና አረንጓዴ ዐሻራ እውን እንዲሆን ጥሪ አቅርበዋል። “ኢትዮጵያውያን በ6ኛው ብሔራዊ ምርጫ ድምፃችንን እንሰጣለን፤ ይህ ምርጫ በሀገሪቱ የመጀመሪያ የሚሆን ነጻ እና ፍትሐዊ ምርጫ እንደሚሆን ተስፋ እናደርጋለን” ብለዋል።
መላው ኢትዮጵያውያን ዴሞክራሲያዊ መብቶችን ለማስከበር ወደ ምርጫው በሚሄዱበት ወቅት ቀኑን የዜግነት ግዴታቸውን በመወጣት የትውልድ ማኅተም ለመተው እንዲጠቀሙበትም ጥሪ አቅርበዋል፡፡ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት “በመጪው ሰኞ ውጡና ድምጽ ስጡ፣ እንዲሁም አረንጓዴ ዐሻራችሁን አስቀምጡ” ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል፡፡ኢትዮጵያውያን አንድ ሆነው ቀኑን ታሪካዊ የዴሞክራሲ ቀን እንዲያደርግትም መልዕክት አስተላልፈዋል።
- Ethiopia Working To Secure New Development Bank MembershipThe Ministry of Foreign Affairs disclosed that Ethiopia is working hard to become member of BRICS’ New Development… Read more: Ethiopia Working To Secure New Development Bank Membership
- የትግራይ ክልል ታጣቂዎች ዳግም ዝርፊያ እያፈጸሙ ነው፤ የተማሪዎች መጽሃፍትን “የአማራ ክልል ናቸው እየሉ ቀደዋል”በአላማጣ ከተማ በተለየ መልኩ የትግራይ ክልል ታጣቂዎች በከተማዋ ውስጥ እንደሚንቀሳቀሱ ነዋሪዎች መመስከራቸውን ቢቢሲ አስታወቀ። ይህ የተገለጸው ከአለማጣ እና… Read more: የትግራይ ክልል ታጣቂዎች ዳግም ዝርፊያ እያፈጸሙ ነው፤ የተማሪዎች መጽሃፍትን “የአማራ ክልል ናቸው እየሉ ቀደዋል”
- በዘንድሮው ዓመት የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ኢትዮጵያ ሰባት ነጥብ ሁለት ቢሊዮን ችግኝ ልትተክል ነውለዘንድሮ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር 6 ነጥብ 5 ቢሊየን ችግኝ ለመትከል ዕቅድ መያዙንna ለዚህም ተግባራዊነት ከሰባት ነጥብ ሁለት ቢሊየን… Read more: በዘንድሮው ዓመት የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ኢትዮጵያ ሰባት ነጥብ ሁለት ቢሊዮን ችግኝ ልትተክል ነው
- አፍሪካ ህብረት ” የውጭ ምንዛሪ ሒሳቡን ወደ ሌላ ሀገር ሊያዘዋውር ነው” የሚለው ዜና ሃሰት መሆኑን አረጋግጠአፍሪካ ህብረት የውጭ ምንዛሬ አካውንቱን ወደ ሌላ አገር እንደሚያዘዋውር ተጠቅሶ በህብረቱ ስም የወጣው ዜና ሃሰት፣ ሆን ተብሎ የተቀነባበረ… Read more: አፍሪካ ህብረት ” የውጭ ምንዛሪ ሒሳቡን ወደ ሌላ ሀገር ሊያዘዋውር ነው” የሚለው ዜና ሃሰት መሆኑን አረጋግጠ
- አፍሪቃ ህብረት ምን አሰጋውና “ገንዘቤን ወደ ሌላ አገር ለማዛወር እያሰብኩ ነው” ሲል ተንሿከከ፤ የጾምና የፍስክ ዜናዎችባንኩ የክፍያ ሰነድ ቀረበለት። ማጣሪያ ጥያቄ ለህብረቱ አቀረበ። ሃሰት ሆኖ ተገኘና ፖሊስ ተጠርጣሪዎቹን ያዘ። ጉዳዩ ወደ ህግ አመራ።… Read more: አፍሪቃ ህብረት ምን አሰጋውና “ገንዘቤን ወደ ሌላ አገር ለማዛወር እያሰብኩ ነው” ሲል ተንሿከከ፤ የጾምና የፍስክ ዜናዎች