ስድስተኛው አገራዊው ምርጫ በሰላም እንዲጠናቀቅ አስፈለጊው ዝግጅት መደረጉ ተጠቆመ ፣”ምርጫውን ለማደናቀፍ፣ የግድቡን ሙሌት ለማስተጓጎል የሚንቀሳቀሱ አሉ፤ ከእይታችን ውጭ ግን አይደሉም” ትብሏል። ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አሕመድ ሕዝብ ወትቶ ያለ ስጋት እንዲመርጥ ጥሪ አቅርበዋል። የፓርቲዎች ሕብረት ምርጫው በሰላማዊ መነግድ እንዲጠናቀቅ አስፈላጊውን ሁሉ እንደሚያደርግ ማስታወቁ አይዘነጋም።
የፌዴራል፣ የክልል የደህንነትና የፀጥታ መዋቅሮች በቂ ዝግጅት ማድረጋቸውን ያስታወቁት የብሔራዊ ደህንነትና መረጃ አገልግሎት ዳይሬክተር ጀነራል አቶ ተመስገን ጥሩነህ ናቸው። የፌዴራል፣ የክልል የደህንነትና የፀጥታ አካላት ግብረኅይል ወቅታዊ የሀገሪቷን ደህንነት የሚገመግም እና ቀጣይ አቅጣጫዎችን የሚያስቀምጥ ውይይት እያደረጉ መሆኑም ታውቋል።
በዚሁ ወቅት የብሔራዊ ደህንነት እና መረጃ አገልግሎት ዳይሬክተር ጀነራል አቶ ተመስገን ጥሩነህ ቀጣዩ የምርጫ እና ድህረ ምርጫ ሰላማዊ እንዲሆን በቂ ዝግጅት እንደተደረገ መናገራቸውን የኢቢሲ ዘግባ አመልክቷል። ምርጫውንና ለማደናቀፍና የግድቡን ሙሌት ለማስተጓጎል የሚሰሩ የውጭ እና የውስጥ ጠላቶች መኖራቸውን የተናገሩት አቶ ተመስገን ሁሉም አይነት እንቅስቃሴ ከደህንነቱ መስሪያ ቤት ክትትል የሚያመልጥ እንዳልሆነ አመልከዋል። ይህንኑ አተናክሮ በአስተማማኝ ለመከወን የፌዴራል፣ የክልል የፀጥታና ደህንነት አካላት የጋራ ግብረ ሀይልም የሀገሪቷን ወቅታዊ የደህንነት ሁኔታ በመገምገም ቀጣይ አቅጣጫዎችን ያስቀምጣሉ ተብሎ ይጠበቃል።
በተመሳሳይ የምርጫ ዜና ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ምርጫና አረንጓዴ ዐሻራ እውን እንዲሆን ጥሪ አቅርበዋል። “ኢትዮጵያውያን በ6ኛው ብሔራዊ ምርጫ ድምፃችንን እንሰጣለን፤ ይህ ምርጫ በሀገሪቱ የመጀመሪያ የሚሆን ነጻ እና ፍትሐዊ ምርጫ እንደሚሆን ተስፋ እናደርጋለን” ብለዋል።
መላው ኢትዮጵያውያን ዴሞክራሲያዊ መብቶችን ለማስከበር ወደ ምርጫው በሚሄዱበት ወቅት ቀኑን የዜግነት ግዴታቸውን በመወጣት የትውልድ ማኅተም ለመተው እንዲጠቀሙበትም ጥሪ አቅርበዋል፡፡ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት “በመጪው ሰኞ ውጡና ድምጽ ስጡ፣ እንዲሁም አረንጓዴ ዐሻራችሁን አስቀምጡ” ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል፡፡ኢትዮጵያውያን አንድ ሆነው ቀኑን ታሪካዊ የዴሞክራሲ ቀን እንዲያደርግትም መልዕክት አስተላልፈዋል።
- ከሱዳን ተፋላሚዎች ጀርባ ትህነግ መኖሩን ጌታቸው ረዳ አረጋገጡ፤ በትግራይ አስተዳደር ስም ማስተባበያም አውጥተዋልበሱዳን ለአንድ ዓመት የዘለቀው የእርስ በእርስ እልቂት ብዙ ተዋንያኖች አሉበት። ከአርቡ ዓለም፣ ከአውሮፓ፣ ከአፍሪቃ፣ ሩሲያና አሜሪካንን ጨምሮ የተለያዩ… Read more: ከሱዳን ተፋላሚዎች ጀርባ ትህነግ መኖሩን ጌታቸው ረዳ አረጋገጡ፤ በትግራይ አስተዳደር ስም ማስተባበያም አውጥተዋል
- Are Tigray mercenaries fighting in conflict-ravaged Sudan?Mercenaries from Ethiopia’s Tigray People’s Liberation Front are fighting alongside Sudanese army regulars against fighters of the Rapid… Read more: Are Tigray mercenaries fighting in conflict-ravaged Sudan?
- Sudan’s RSF Accuse Tigray People’s Liberation Front of Backing SAFSudanese warring party Rapid Support Forces has officially accused the Tigray People’s Liberation Front Fighters of fighting in… Read more: Sudan’s RSF Accuse Tigray People’s Liberation Front of Backing SAF
- የኢትዮጵያን – “መከራዋን ካልተሸከምንላት ኢትዮጵያዊነቱ ምኑ ላይ ነው” አብይ አሕመድ“ኢትዮጵያ ኢትዮጵያ” እያሉ በስሟ ሲምሉ የነበሩ ብዙዎች ነበሩ፤ ከልባቸው ለቃላቸው ታምነው ልጅ የሆኗት ግን ጥቂቶች ብቻ ናቸው። አንዳንዶች… Read more: የኢትዮጵያን – “መከራዋን ካልተሸከምንላት ኢትዮጵያዊነቱ ምኑ ላይ ነው” አብይ አሕመድ
- አቡነ አብርሃም “እንዳይረፍድብን” ሲሉ ለመጸጸት እንኳን ዕድል እንዳይታጣ አስጠነቀቁ“ወገኖቼ እንማርና እናስተምር፣ ወንጀልን እንጸየፈው፣ እንጥላው፣ ወንጀልን ተጸይፈን ወንጌልን እንውደደው፣ በወንጌል እንኑር፣ ወንጌል ሕጓም ስርዓቷም ያማረች ናት፤ ወንጌላዊ… Read more: አቡነ አብርሃም “እንዳይረፍድብን” ሲሉ ለመጸጸት እንኳን ዕድል እንዳይታጣ አስጠነቀቁ