Site icon ETHIO12.COM

ከሩብ ቢሊዮን ብር በላይ የታቀፈቸው ” የትህነግ መሪ” ሰንሰለታማ የዝርፊያ ድራማ

የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ሆኖ ለማንም በማይገባ ምክንያት አፋራና አማራን ወሮ የያዘው ቡድን መሪ የሆኑት ወ/ሮ ፈትለወርቅ ገብረ እግዚአብሄር የፋይናንስ መረጃ ደህንነት ምክትል ዳይሬክተር በነበሩበት ወቅት 267 ሚሊዮን ብር በወንዳምቸው ዳዊት ገብረ እግዚአብሄር ስም ንግድ ባንክ መግባቱን ጠንቅቀው ያውቃሉ። ጨዋታው የሚጀምረው እዚህ ላይ ነው።

አቶ ዳዊት ይህን ያክል ብር በአንዴ ንግድ ባንክ ሲያስቀምጡ ” ከየት አመጡ” አልተባለም። ገንዘቡ ረሽም ጊዜ ባንክ መቀመጡ ደግሞ “ለምን?” የሚል ጥያቄ ያስነሳል። ቀጥሎ አቶ ቱሉ ጣፋ ድራማውን መሪ ሆነው ብቅ ይላሉ። አቶ ቱሉ ይህን ሁሉ ብር ለመውሰድ ሲመቻቹ አንድ በባለሙያዎችና በህግ ሰዎች የተመከረበት ሰንሰለት ይዘጋጃል።

የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ከፋይናንስ ደህንነት አገልግሎት ጋር በመተባበር እንደደረሰበትና እንዳመከነው የገለጸው የወንጀል ሪፖርት እንደሚያስረዳው ድራማው የተዋቀረው ከቀበሌ ጀምሮ ነው። ዋናው አስተኳሾች ግን የተደራጁ የባንክ ሰራተኞች ናቸው።

የፋይናንስና ንግድ ወንጀሎች ምርመራ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ረዳት ኮሚሽነር ብርሃኑ ገለጻ አቶ ዳዊት 276 ሚሊዮን ብር ንግድ ባንክ እንዳላቸው መረጃውን ለሰነሰለቱ ሰዎች ያቀበሉት የባንክ ሰዎች ናቸው። የባንክ ሰዎቹ በሰጡት መረጃ መሰረት በህጋዊ መንገድ ብሩን ወደ አቶ ቱሉ አካውንት ለማዞር በቡና ባንክ አዲስ የሂሳብ ደብተር ይዘጋጃል።

አቶ ቱሉ 121 ሰዎች መታወቂያ እንዲወስዱ በተደረገበት ቤት ተመዝግበው የነዋሪነት ማረጋገጫ ያገኛሉ። በዛው መታወቂያ አድራሻ ህጋዊ ሆነው የህግ ሰዎች በሚያስቀምጡት የአሰራር ሂደት መሰረት ስራው ይጀመራል።

አቶ ቱሉ ከአቶ ዳዊት ጋር የስራ ውል እንደነበራቸው ተደርጎ የተቀናበረው ሰነድ በግልግል ዳኝነት ህጋዊ ውሳኔ እንደተሰጠው አስመስሎ በማቅረብና በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የአፈፃፀም ችሎት እንዲከፈት በማድረግ በህገ-ወጥ መንገድ ገንዘብ ለመውሰድ ጨዋታው ይጀመራል። ተጀምሮም አክተሮች እየጨመረ ወደ መገባደጃው ያመራል።

ክብሮም ወልዱ በሚባሉ በአካል በሌሉና በማይታወቁ ሰው ተወስኖ ቀርቧል የተባለው የግልግል ውሳኔ አግባብነት የሌለው መሆኑ እየታወቀ ” ቅድሚያ መደለያ 400 ሺህ ብር ተቀበሉ” የተባሉ ዳኛ አፈጻጸም እንዲከፈት ያዛሉ። ሂደቱ እዚህ ሲደርስ አቶ ቱሉ በተዘጋጀላቸው ደረቅ ቼክ ለሌሎች የሰንሰለቱ ተባባሪዎች ዳኞችን ጨምሮ ብሩ ሲለቀቅ የሚሰጡትን ገንዘብ በመጻፍ ቼክ ያድላሉ። ፖሊስ እንዳለው።

ትክክል አለመሆኑን እያወቁ በመምሳጠር “ትክክል ነው” በማለት በወንጀሉ የተሳተፉ ሌሎች ግብረ አበሮች ሐምሌ 16 ቀን 2013 ዓ.ም አፈፃፀም እንዲከፈት ፍርድ ቤት በጠየቁት መሰረት ጉዳዩ የቀረበለት የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት 11ኛ ወንጀል ችሎት ሲሆን የተጠየቀው ጥያቄ የፍርድ ባለመብት ተብሎ የቀረበው ቱሉ ጣፋ በዳዳ የሚባል ግለሰብ ሲሆን የፍርድ ባለ እዳ ሆኖ የቀረበው ተጠርጣሪ ዳዊት ገ/እግዝሐብሔር መሆናቸው ተዘርዝራል።

ረቂቅ ዜናዊ የምትባልና አሁን ለጊዜው አገር ቤት የለችም የተባለች ተጠርጣሪ የአቶ ዳዊት ወኪል በመሆን አቶ ቱሉ ላቀረቡት የበደል ጥያቄ ደጋፊና እማኝ መሆናቸውን ፖሊስ አውስቷል።

ከዚህ በፊት ሁለቱ ግለሰቦች የስራ ግንኙነት ያላቸው በማስመሰል የብድር ውል በማቅረብ ገንዘቡን አልከፈለልኝም በማለት ወደ ገላጋይ ዳኛ ወስደው ክርክር እንዳደረጉ፣ የተጠየቀው 276 ሚሊየን ብር አቶ ዳዊት ገ/እግዝሐብሔር በተባሉት ስም በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሚገኝ ገንዘብ በወንጀሉ የተሳተፉ ተጠርጣሪዎች ሌሎች መረጃ የሚሰጡ ግለሰቦችን በመጠቀም የባንክ ሂሳብ ደብተሩ ላይ ያለውን የገንዘብ መጠን ካጠኑ በኋላ ለመውሰድ ሙከራ ማድረጋቸውን፣ ይህንኑ የተቀነባበረ ወንጀል ፖሊስ ሲከታተለው እንደነበር፣ በመጨረሻም ከሚፈለጉት አስራ ሶስት ተጠርጣሪዎች አስሩ መያዝቸውን ረዳት ኮሚሽነሩ አስታወቀዋል።

ፖሊስ ይህን ያህል ብር በአንድ ጊዜ ባንክ ገብቶ ለረዥም ጊዜ መቀመጡና ንብረቱ ደግሞ የወይዘሮ ፈትለወርቅ ወንድም መሆኑ ፖሊስ ምርመራውን እንዲያሰፋ አስችሎታል። ፖሊስ እንዳለው አቶ ቱሉ ፊት ሆነው ድራማውን እንዲሰሩት ይደረጉ እንጂ ገንዘቡ ለትህነግ ሽብር ተግባር ሊተላለፍ እንደነበር ጥርጣሬው ሰፊ ነው። የአቶ ዳዊት ህጋዊ ወኪል የተባሉ ረቂቅ ዜናዊ ከአገር መውጣታቸው ሪፖርቱ ሲቀርብ ተመልክቷል።


ምን ያክል ተዘጋጅተናል? ጥድፊያ አገር አልባ ለመሆን !! ህጻናቱ ምን አጠፉ?
ያለፈውን ግማሽ ምዕተ ዓመት የኢትዮጵያ ፖለቲካ እና ሥነ መንግሥት ታሪክ በጥሞና የተከታተለ …
የደም ግፊት በመለካትና ክትትል በማድረግ የስትሮክ ተጋላጭነትን መቀነስ
 አንድ ሰው የደም ግፊት መጠኑ ከፍተኛ ከሆነ እና በጊዜው ሕክምና ካላደረገ ለከፍተኛ …
የስኳር ህመም አይነቶች እና ምልክቶች
የስኳር ህመም በደም ውስጥ የስኳር መጠን ከሚገባው በላይ ሆኖ በሚገኝበት ሰዓት የሚከሰት …
ማንኮራፋትና ትዳርን እስከ ማፍረስ የሚያደርሰው መዘዙ ? ማንኮራፋት መፍትሄ አለው?
የማንኮራፍት መዘዙ እንቅልፍ ማሳጣት ብቻ አይደለም። ማንኮራፋት ከሚያንኮራፉት ሰዎች ጎን በሚተኙ ሰዎች …
Ethiopia Working To Secure New Development Bank Membership
The Ministry of Foreign Affairs disclosed that Ethiopia is working hard to …
የትግራይ ክልል ታጣቂዎች ዳግም ዝርፊያ እያፈጸሙ ነው፤ የተማሪዎች መጽሃፍትን “የአማራ ክልል ናቸው እየሉ ቀደዋል”
በአላማጣ ከተማ በተለየ መልኩ የትግራይ ክልል ታጣቂዎች በከተማዋ ውስጥ እንደሚንቀሳቀሱ ነዋሪዎች መመስከራቸውን …
Exit mobile version