ጳግሜን 5 የትውልድ ቀን “ኢትዮጵያ የትውልድ ምድር” በሚል መሪ ሃሳብ በፌዴራል ደረጃ በውይይት እና ሌሎች ዝግጅቶች ተከብሯል፡፡ “በትውልዶች መካከል ቅብብል ወይስ ቅራኔ” በሚል ርእስ ለውይይት መነሻ የሚኾን ጥናታዊ ጽሑፍ ቀርቧል፡፡
ኢትዮጵያ ለዘመናት በጸናው ታሪኳ እና ዘርፈ ብዙ አውድን ባስተናገደው የሀገረ መንግሥቷ ምስረታ አያሌ የሚባሉ ውጣ ውረዶችን አስተናግዳለች፡፡ ሀገር እንደውርስ በትናንት፣ በዛሬ እና በነገ መካከል ስትጸና፤ እዳ እና ምንዳ ደግሞ ትውልድ በየጊዜው የሚረካከበው እና የሚያወራርደው ነገር ኾኗል ይላሉ፡፡
ትውልድ የሚለው ስያሜ ተፈጥሯዊ ከኾነው ብያኔ በዘለለ የማኅበራዊ፣ ፖለቲካዊ፣ ምጣኔ ሃብታዊ እና ባሕላዊ ክስተት መገለጫም ኾኖ ያገለግላል ያሉት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካል ሳይንስ እና ዓለም አቀፍ ግንኙነቶች ትምህርት ክፍል ተመራማሪ፣ መምህር እና የጥናታዊ ጽሑፉ አቅራቢ ዮናስ አሸኔ (ዶ.ር) ናቸው፡፡
በጥናታዊ ጽሑፋቸው ነገረ-ትውልድ ፣ የትውልድ ክፍፍል ፣ ፋና ወጊ ትውልድ እና በትውልድ መካከል ቅብብል ወይስ ቅራኔ የሚሉ ነጥቦችን ያነሱት ዶክተር ዮናስ በትውልዶች መካከል የተለያየ እና የተሳሰረ ቅብብሎሽ እና ቅራኔ ሊኖር እንደሚችል ማሳያዎችን ጠቅሰው አንስተዋል፡፡
የፖለቲካል ሳይንስ ምሑሩ ትውልድ ከተፈጥሯዊ ብያኔው በዘለለ ለክስተት የሚሰጥ መለያ እና ትስስር ተደርጎ እንደሚወሰድም አንስተዋል፡፡ በኢትዮጵያ የፖለቲካ ታሪክ ውስጥ “የ1960ዎቹ” ትውልድ በተደጋጋሚ የሚጠራ የአንድ ትውልድ መለያ ነው የሚሉት ዶክተር ዮናስ ይኽም ከማኅበራዊ ሱታፌ የፖለቲካ ርእዮተ ዓለም እና ከአቢዮት ጋር የተያያዘ እንደነበር አንስተዋል፡፡ በዚያ ዘመን የነበረው ትውልድ ያሳያቸው ባህሪያት እና የተጋፈጣቸው ክስተቶች ነበሩ፡፡ ያ ትውልድ እስከ አሁኑ ትውልድ ድረስ የዚያ ዘመን መንፈስ እና ጽንሰ ሃሳብ መገለጫ ኾኖ ይጠራል ነው ያሉት፡፡
ትውልድ በባህሪው ተከታታይ፣ ቀጣይነት ያለው እና የተንሰላሰለ በመኾኑ የተለያዩ ተከታታይ ትውልዶች ብዙውን ጊዜ ተመሳሳይ ንቃተ ህሊና ይጋራሉ የሚሉት ጥናታዊ ጽሑፍ አቅራቢው ከ1960ዎቹ ትውልድ ጀምሮ የተስተዋለውን ብሔርተኝነት በማሳያነት አቅርበዋል፡፡ ይህም በጊዜ፣ በታሪክ እና በባሕል መካከል ያለውን ግንኙነት እና ትስስር የሚያመላክት እንደኾነ ተነስቷል፡፡
እያንዳንዱ ትውልድ የሚጓዘው በአንድ መርከብ ውስጥ ቢኾንም የራሱ ትናንት፣ ዛሬ እና ነገ አለው ያሉት ዶክተር ዮናስ “ዘመን ትውልድን ይገነባል፤ ትውልድም ዘመንን ይገነባል” ነው ያሉት፡፡ “በትውልዶች መካከል ቅብብል ወይስ ቅራኔ” የሚለው ጥያቄም እያንዳንዱ ትውልድ በሚገነባው የራሱ ዘመን ውስጥ የሚቀበለውን ምንዳ እና የሚከፍለውን እዳ ለመጠየቅ ነው ብለዋል፡፡
በትናንቱ እና በአሁኑ ትውልድ መካከል ትዝታ፣ ትውስታ፣ ተረኮች፣ ታሪኮች እና የባሕል መገለጫዎች በፖለቲካዊ ክስተቶች ላይ ተፅዕኖ የሚፈጥሩ ውርሶች ናቸው፡፡ የትኛውም ትናንት ለአሁኑ ትውልድ ህልም ግንባታ ይጠቅማል እና ነገን እንዴት ይገነባል የሚሉት ጥያቄዎች መጻዒውን እንደሚወስኑ በጥናታዊ ጽሑፉ ቀርቧል፡፡ አሁናዊውን የኢትዮጵያ ነባራዊ ኹኔታ በማስመልከትም ትውልዱ ሀገረ-መንግሥት ፋና ወጊ፣ አብዮታዊ ፋና ወጊ እና ድህረ አብዮት ወራሽ ትውልድ ተብሎ ተንሰላስሏል፡፡
የጥናታዊ ጽሑፍ አቅራቢው እንደመውጫም በኢትዮጵያ የፖለቲካ ትውልድ መካከል ነገረ-ጠመንጃን፣ አሸናፊና ተሸናፊ እንዲሁም ውርስና መነቀል አሁንም ድረስ ፈታኝ ክስተቶች መኾናቸውን አንስተው የጠመንጃን ጉዳይ ቋጭቶ የሲቪል ፖለቲካ ምህዳሩን ማስፋት እንደሚያስፈልግ አንስተዋል፡፡
ዘጋቢ፡- ታዘብ አራጋው (አሚኮ)
- “አሜሪካን አገር ሆነው የኢትዮጵያ ሰላም የሚያውኩ ተላልፈው ይሰጡኝ” ፖሊስ በኤርቪን ማሲንጋን በኩል ጥያቄ አቀረበአሜሪካ ተቀምጠው የኢትዮጵያን ሰላም የሚያውኩ ተፈላጊዎችን ሀገሪቱ አሳልፋ በመስጠት ትብብር እንድታደርግ የፌደራል ፖሊስ መጠየቁ ተገለጸ። በጀርመን በተመሳሳይ ስራ መጀመሩ የሚታወስ… Read more: “አሜሪካን አገር ሆነው የኢትዮጵያ ሰላም የሚያውኩ ተላልፈው ይሰጡኝ” ፖሊስ በኤርቪን ማሲንጋን በኩል ጥያቄ አቀረበ
- ሃሰተኛ የተባሉ የዩቲዩበር ባለቤቶች ተያዙ፤ በአንድ ተጠርጣሪ ብቻ ስምንት የዩቲዩብ ቻናል ተከፍቷልፈቃድ ሳይኖራቸው በየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ ስምንት አማረ እና ቤተሰቦቹ በተባለ ህንፃ ላይ ቢሮ ተከራይተው ሃሰተኛና የፈጠራ ወሬ ሲያሰራጩ ነበሩ… Read more: ሃሰተኛ የተባሉ የዩቲዩበር ባለቤቶች ተያዙ፤ በአንድ ተጠርጣሪ ብቻ ስምንት የዩቲዩብ ቻናል ተከፍቷል
- “ከሱዳን ተፋላሚዎች ጀርባ ትህነግ መኖሩን ጌታቸው ረዳ አረጋግጠዋል”፤ የሚለው ዜና የአማራ ፖለቲካን ቀየረበሱዳን ለአንድ ዓመት የዘለቀው የእርስ በእርስ እልቂት ብዙ ተዋንያኖች አሉበት። ከአርቡ ዓለም፣ ከአውሮፓ፣ ከአፍሪቃ፣ ሩሲያና አሜሪካንን ጨምሮ የተለያዩ አካላት የሚዳክሩበት… Read more: “ከሱዳን ተፋላሚዎች ጀርባ ትህነግ መኖሩን ጌታቸው ረዳ አረጋግጠዋል”፤ የሚለው ዜና የአማራ ፖለቲካን ቀየረ
- Are Tigray mercenaries fighting in conflict-ravaged Sudan?Mercenaries from Ethiopia’s Tigray People’s Liberation Front are fighting alongside Sudanese army regulars against fighters of the Rapid Support Forces… Read more: Are Tigray mercenaries fighting in conflict-ravaged Sudan?
- Sudan’s RSF Accuse Tigray People’s Liberation Front of Backing SAFSudanese warring party Rapid Support Forces has officially accused the Tigray People’s Liberation Front Fighters of fighting in Sudan in… Read more: Sudan’s RSF Accuse Tigray People’s Liberation Front of Backing SAF