ጳግሜን 5 የትውልድ ቀን “ኢትዮጵያ የትውልድ ምድር” በሚል መሪ ሃሳብ በፌዴራል ደረጃ በውይይት እና ሌሎች ዝግጅቶች ተከብሯል፡፡ “በትውልዶች መካከል ቅብብል ወይስ ቅራኔ” በሚል ርእስ ለውይይት መነሻ የሚኾን ጥናታዊ ጽሑፍ ቀርቧል፡፡
ኢትዮጵያ ለዘመናት በጸናው ታሪኳ እና ዘርፈ ብዙ አውድን ባስተናገደው የሀገረ መንግሥቷ ምስረታ አያሌ የሚባሉ ውጣ ውረዶችን አስተናግዳለች፡፡ ሀገር እንደውርስ በትናንት፣ በዛሬ እና በነገ መካከል ስትጸና፤ እዳ እና ምንዳ ደግሞ ትውልድ በየጊዜው የሚረካከበው እና የሚያወራርደው ነገር ኾኗል ይላሉ፡፡
ትውልድ የሚለው ስያሜ ተፈጥሯዊ ከኾነው ብያኔ በዘለለ የማኅበራዊ፣ ፖለቲካዊ፣ ምጣኔ ሃብታዊ እና ባሕላዊ ክስተት መገለጫም ኾኖ ያገለግላል ያሉት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካል ሳይንስ እና ዓለም አቀፍ ግንኙነቶች ትምህርት ክፍል ተመራማሪ፣ መምህር እና የጥናታዊ ጽሑፉ አቅራቢ ዮናስ አሸኔ (ዶ.ር) ናቸው፡፡
በጥናታዊ ጽሑፋቸው ነገረ-ትውልድ ፣ የትውልድ ክፍፍል ፣ ፋና ወጊ ትውልድ እና በትውልድ መካከል ቅብብል ወይስ ቅራኔ የሚሉ ነጥቦችን ያነሱት ዶክተር ዮናስ በትውልዶች መካከል የተለያየ እና የተሳሰረ ቅብብሎሽ እና ቅራኔ ሊኖር እንደሚችል ማሳያዎችን ጠቅሰው አንስተዋል፡፡
የፖለቲካል ሳይንስ ምሑሩ ትውልድ ከተፈጥሯዊ ብያኔው በዘለለ ለክስተት የሚሰጥ መለያ እና ትስስር ተደርጎ እንደሚወሰድም አንስተዋል፡፡ በኢትዮጵያ የፖለቲካ ታሪክ ውስጥ “የ1960ዎቹ” ትውልድ በተደጋጋሚ የሚጠራ የአንድ ትውልድ መለያ ነው የሚሉት ዶክተር ዮናስ ይኽም ከማኅበራዊ ሱታፌ የፖለቲካ ርእዮተ ዓለም እና ከአቢዮት ጋር የተያያዘ እንደነበር አንስተዋል፡፡ በዚያ ዘመን የነበረው ትውልድ ያሳያቸው ባህሪያት እና የተጋፈጣቸው ክስተቶች ነበሩ፡፡ ያ ትውልድ እስከ አሁኑ ትውልድ ድረስ የዚያ ዘመን መንፈስ እና ጽንሰ ሃሳብ መገለጫ ኾኖ ይጠራል ነው ያሉት፡፡
ትውልድ በባህሪው ተከታታይ፣ ቀጣይነት ያለው እና የተንሰላሰለ በመኾኑ የተለያዩ ተከታታይ ትውልዶች ብዙውን ጊዜ ተመሳሳይ ንቃተ ህሊና ይጋራሉ የሚሉት ጥናታዊ ጽሑፍ አቅራቢው ከ1960ዎቹ ትውልድ ጀምሮ የተስተዋለውን ብሔርተኝነት በማሳያነት አቅርበዋል፡፡ ይህም በጊዜ፣ በታሪክ እና በባሕል መካከል ያለውን ግንኙነት እና ትስስር የሚያመላክት እንደኾነ ተነስቷል፡፡
እያንዳንዱ ትውልድ የሚጓዘው በአንድ መርከብ ውስጥ ቢኾንም የራሱ ትናንት፣ ዛሬ እና ነገ አለው ያሉት ዶክተር ዮናስ “ዘመን ትውልድን ይገነባል፤ ትውልድም ዘመንን ይገነባል” ነው ያሉት፡፡ “በትውልዶች መካከል ቅብብል ወይስ ቅራኔ” የሚለው ጥያቄም እያንዳንዱ ትውልድ በሚገነባው የራሱ ዘመን ውስጥ የሚቀበለውን ምንዳ እና የሚከፍለውን እዳ ለመጠየቅ ነው ብለዋል፡፡
በትናንቱ እና በአሁኑ ትውልድ መካከል ትዝታ፣ ትውስታ፣ ተረኮች፣ ታሪኮች እና የባሕል መገለጫዎች በፖለቲካዊ ክስተቶች ላይ ተፅዕኖ የሚፈጥሩ ውርሶች ናቸው፡፡ የትኛውም ትናንት ለአሁኑ ትውልድ ህልም ግንባታ ይጠቅማል እና ነገን እንዴት ይገነባል የሚሉት ጥያቄዎች መጻዒውን እንደሚወስኑ በጥናታዊ ጽሑፉ ቀርቧል፡፡ አሁናዊውን የኢትዮጵያ ነባራዊ ኹኔታ በማስመልከትም ትውልዱ ሀገረ-መንግሥት ፋና ወጊ፣ አብዮታዊ ፋና ወጊ እና ድህረ አብዮት ወራሽ ትውልድ ተብሎ ተንሰላስሏል፡፡
የጥናታዊ ጽሑፍ አቅራቢው እንደመውጫም በኢትዮጵያ የፖለቲካ ትውልድ መካከል ነገረ-ጠመንጃን፣ አሸናፊና ተሸናፊ እንዲሁም ውርስና መነቀል አሁንም ድረስ ፈታኝ ክስተቶች መኾናቸውን አንስተው የጠመንጃን ጉዳይ ቋጭቶ የሲቪል ፖለቲካ ምህዳሩን ማስፋት እንደሚያስፈልግ አንስተዋል፡፡
ዘጋቢ፡- ታዘብ አራጋው (አሚኮ)
- የበርሊን ማራቶን ባለማዕረግ ትግስት እነ ዱቤ ጂሎ ቢሳተፉ ታዝረከርካቸው ነበርበማራቶን ከሁለት ደቂቃ በላይ ማሻሻል እጅግ የሚደነቅና ያልተለመደ ነው። ባለሙያዎቹ ወይም አሰልጣኞቹ የሮጠችበትን ፍጥነት በሰዓትና ርቀት ከፋፍለው ቢያቀርቡት ምን አልባትም ወንዶችን የሚገዳደር ፍጥነት ተጠቅማ ሮጣለች። የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ተቴክኒክ ዳይሬክተርና የአትሌቶች ኮሚሽን ሰብሳቢ የነበሩት የዛሬው የተከበሩ ዱቤ ጅሎ አይነቱን ሯጮችን አዝረክርኮ ማሸነፍ የሚያስችላትን ሃይል አሳይታለች። የበርሊና ባለ ማዕረግ ትዕግስት!! ተግስት … Read moreContinue Reading
- የባህር ዳር ነዋሪዎች- ኢትዮጵያን ዜጎች በሁሉም ቦታ እኩል የሚስተናገዱባት ሀገር ማድረግ ይገባልየባህር ዳር ነዋሪዎች የሕዝብን ጥያቄ የመፍታት አቅም፣ ፍላጎት እና ቅንነት ያለው አመራር በመፍጠር ሕዝብን መካስ እንደሚያስፈልግ፣ ኢትዮጵያ በዘር ከመገፋፋት እና ከመጠቃቃት ነጻ የኾነች ፣ዜጎች በሁሉም ቦታ እኩል የሚስተናገዱባት ሀገር እንድትኾን ማድረግና የፌዴራል መንግሥት የአማራ ሕዝብ ኅብረ ብሔራዊ እና ልማት ወዳድ እንጅ ጦርነትን የማይፈልግ መኾኑን በውል በመገንዘብ የሕዝቡን ተዘዋውሮ የመሥራት እና … Read moreContinue Reading
- ለወልቃይት ጠገዴ ሴቲት ሁመራ አንድ ሚሊዮን የጉልበት ሰራተኛ ይፈለጋል፤ ከአንድ ነጥን አንድ ሚሊዮን ኩንታል በላይ ሰሊጥ ይጠበቃል“ከየትኛውም የኢትዮጵያ ክልል አስተማማኝ ሰላም ያለው እዚህ ነው። ለሰራተኞች እንደ ቤተሰብ ዝግጅት አድርገናል። ኑ” ሲሉ የተሰሙት አምስት መቶና ሶስት መቶ ሄክታር ሰሊጥና ማሽላ ያመረቱ ባለሃብቶች ናቸው። የዞኑ ግብርና ቢሮ ሃላፊ እንዳሉት አንድ ሚሊዮን አንድ መቶ ሃምሳ ሁለት ሺህ ኩንታል የሰሊጥ ምርት ስለሚጠበቅ ከአንድ ሚሊዮን በላይ የሰራተኛ ሃይል ያስፈልጋል። የዞኑ አርባ … Read moreContinue Reading
- የጎንደርን ከተማ ምን አይነት ተኩስ እንደሌለ ተገለጸ፤ ጎንደር ተይዛለች ተብሎ ነበር“ጎንደር ከተማን ሙሉ በሙሉ ይዘናታል” ሲሉ ስማቸው እንዳይገለጽ ጠይቀው ለጀርመን ድምጽ መረጃ በሰጡ የአማራ ሕዝባዊ ኃይል ፋኖ ቃል አቀባይ አየር ማረፊያውን ሆን ብለው እንዳልያዙ አመልክተዋል። እሳቸው ተናገሩ የተባለው በጀርመን ድምጽ እየተሰማ በለበት ሰዓት በተመሳሳይ የጎንደር ከተማ አስተዳደር ውጊያ መደረጉን ሳያስተባብል ከተማዋን ለመያዝ የገባው ሃይል መደምሰሱን አሃዝ ጠቅሶ አመልክቷል። አገር መከላከያም … Read moreContinue Reading
- “የሞተው ባልሽ ገዳዩ ወንድምሽ፣ሀዘንሽ ቅጥ አጣ ከቤትሽ አልወጣ”የሞተው ባልሽ ገዳዩ ወንድምሽ (ሀዘንሽ ቅጥ አጣ ከቤትሽ አልወጣ) የሚለው የቆየ ተረት ልብን የሚያደማ ኩነትን ማሳያ ነው። እቺ መከረኛ ሚስት ባልዋ በእናቷ ልጅ ወንድሟ ተገደለ። ሟች ባል፣ ገዳይ ወንድም … ኢህአፓ “ሃይማኖት ነው” በሚል ሲገልጸው በነበረው ትግል በቀይና ነጭ ሽብር ስም እናቶች የወላድ መካን ሆነዋል። ጧሪ ያጡና ባዶ ቤት ሃዘን … Read moreContinue Reading