ትናንት ከሀገር ፍቅር እና ደመ ሞቃትነት የተነሳ አንድ ትውልድ በሚባል መልኩ ዋጋ ከፍሏል። ከዚያ መማር የዚህ ትውልድ የቤት ሥራ ነው፡፡ ሀገርን መጠበቅ፣ ሥልጣኔን ማስቀጠል እና ውስብስብ የኾነውን ዓለም ተረድተው መውጫ ብልሃት የሚያመነጩ ልጆችን ኢትዮጵያ ትፈልጋለች ። እኛ ከእኛ የተሻለ ትውልድ መፍጠር ካልቻልን ሀገር እየገደልን ነው” ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ
ጳግሜን 5 የትውልድ ቀን ” ኢትዮጵያ የትውልዶች ድምር” በሚል መሪ ሃሳብ በፌዴራል ደረጃ እየተከበረ ነው፡፡ ትምህርት ሚኒስቴር፣ የሴቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር እና ፍትሕ ሚኒስቴር በጋራ ባዘጋጁት የትውልድ ቀን በዓል ላይ ፕሬዚዳንት ሳህለ ወርቅ ዘውዴን ጨምሮ አርበኞች፣ አረጋዊያን እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል፡፡
በመርሐ ግብሩ ላይ ተገኝተው ለበዓሉ ታዳሚዎች መልእክት ያስተላለፉት የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የአሁኑ ትውልድ ካለፈው የሚማር እና ለሚመጣው የሚያስተምር መደላድል ነው ብለዋል፡፡ በአዲስ ዓመት ዋዜማ ላይ ቆመን ያለፈውን እና የሚመጣውን ስናስብ ለነገ ተስፋ የምናይበት ነው ብለዋል፡፡
ሽግግሩ የአንድ ዓመት ብቻ ሳይኾን በርካታ ዘመናትን አስታውሰን፤ እልፍ ዘመናትን የምንቀበልበት ነው ያሉት ፕሮፌሰር ብርሃኑ የእርሳቸው ትውልድ በርካታ ጥሩ ነገሮች እንዳሉት አንስተው አሁናዊው ትውልድ ሊማርበት የሚገባ በርካታ ጉድለቶች ነበሩበት ብለዋል፡፡ ሀገር ወዳድነት፣ ማንበብ፣ ማሰብና ማንሰላሰል እንዲሁም ምክንያታዊነት የዚያ ዘመን በጎ ጎኖች ነበሩ ብለዋል፡፡
“የእኛ ትውልድ የትግሉ ማዕከል ሀገሩ ነበረች” ያሉት የትምህርት ሚኒስትሩ ነገር ግን ዓለምን የምንመለከትበት መነጽር ጠባብ በመኾኑ በርካታ ዋጋ ከፍለናል ብለዋል፡፡ አንድ ፖለቲካዊ ርዕዮተ ዓለም እንደ መታገያ መስመር መውሰድ እና እርሱን ብቻ መፍትሔ አድርጎ መመልከት ድክመት ነበር፤ የሀገሪቱን ነባራዊ ሁኔታ ከግምት ውስጥ አለማስገባትም ዋጋ አስከፍሏል ብለዋል፡፡
ትናንት ከሀገር ፍቅር እና ደመ ሞቃትነት የተነሳ አንድ ትውልድ በሚባል መልኩ ዋጋ ከፍሏል ያሉት ፕሮፌሰር ብርሃኑ ከዚያ መማር የዚህ ትውልድ የቤት ሥራ ነው ብለዋል፡፡ ሀገርን መጠበቅ፣ ሥልጣኔን ማስቀጠል እና ውስብስብ የኾነውን ዓለም ተረድተው መውጫ ብልሃት የሚያመነጩ ልጆችን ኢትዮጵያ ትፈልጋለች ነው ያሉት፡፡
ሚኒስትሩ በንግግራቸው ላለፉት ሦስት አስርት ዓመታት ትውልዱ የተወዛገበ የሞራል መሰረት ላይ መቆሙን ጠቁመው፤ “እኛ ከእኛ የተሻለ ትውልድ መፍጠር ካልቻልን ሀገር እየገደልን ነው” ብለዋል፡፡ ትምህርት ሚኒስቴር በቅርቡ እየፈጸማቸው ያሉ የሥርዓተ-ትምህርት ማሻሻያ እና የትምህርት ፍኖተ ካርታ ትግበራ ዓላማው ተማሪዎችን መጣል ሳይኾን ራሱን ችሎ የሚቆም ትውልድ ማፍራት እንደኾነ አንስተዋል፡፡
በጎ፣ ግብረ-ገብ፣ አንሰላሳይ፣ አሳቢ፣ ምክንያታዊ እና ትጉህ ተማሪ ለማፍራት ኢትዮጵያዊያን በጋራ እንዲቆሙም ሚኒስትሩ ጥሪ አቅርበዋል፡፡
ዘጋቢ፡- ታዘብ አራጋው አሚኮ
- የበርሊን ማራቶን ባለማዕረግ ትግስት እነ ዱቤ ጂሎ ቢሳተፉ ታዝረከርካቸው ነበርበማራቶን ከሁለት ደቂቃ በላይ ማሻሻል እጅግ የሚደነቅና ያልተለመደ ነው። ባለሙያዎቹ ወይም አሰልጣኞቹ የሮጠችበትን ፍጥነት በሰዓትና ርቀት ከፋፍለው ቢያቀርቡት ምን አልባትም ወንዶችን የሚገዳደር ፍጥነት ተጠቅማ ሮጣለች። የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ተቴክኒክ ዳይሬክተርና የአትሌቶች ኮሚሽን ሰብሳቢ የነበሩት የዛሬው የተከበሩ ዱቤ ጅሎ አይነቱን ሯጮችን አዝረክርኮ ማሸነፍ የሚያስችላትን ሃይል አሳይታለች። የበርሊና ባለ ማዕረግ ትዕግስት!! ተግስት … Read moreContinue Reading
- የባህር ዳር ነዋሪዎች- ኢትዮጵያን ዜጎች በሁሉም ቦታ እኩል የሚስተናገዱባት ሀገር ማድረግ ይገባልየባህር ዳር ነዋሪዎች የሕዝብን ጥያቄ የመፍታት አቅም፣ ፍላጎት እና ቅንነት ያለው አመራር በመፍጠር ሕዝብን መካስ እንደሚያስፈልግ፣ ኢትዮጵያ በዘር ከመገፋፋት እና ከመጠቃቃት ነጻ የኾነች ፣ዜጎች በሁሉም ቦታ እኩል የሚስተናገዱባት ሀገር እንድትኾን ማድረግና የፌዴራል መንግሥት የአማራ ሕዝብ ኅብረ ብሔራዊ እና ልማት ወዳድ እንጅ ጦርነትን የማይፈልግ መኾኑን በውል በመገንዘብ የሕዝቡን ተዘዋውሮ የመሥራት እና … Read moreContinue Reading
- ለወልቃይት ጠገዴ ሴቲት ሁመራ አንድ ሚሊዮን የጉልበት ሰራተኛ ይፈለጋል፤ ከአንድ ነጥን አንድ ሚሊዮን ኩንታል በላይ ሰሊጥ ይጠበቃል“ከየትኛውም የኢትዮጵያ ክልል አስተማማኝ ሰላም ያለው እዚህ ነው። ለሰራተኞች እንደ ቤተሰብ ዝግጅት አድርገናል። ኑ” ሲሉ የተሰሙት አምስት መቶና ሶስት መቶ ሄክታር ሰሊጥና ማሽላ ያመረቱ ባለሃብቶች ናቸው። የዞኑ ግብርና ቢሮ ሃላፊ እንዳሉት አንድ ሚሊዮን አንድ መቶ ሃምሳ ሁለት ሺህ ኩንታል የሰሊጥ ምርት ስለሚጠበቅ ከአንድ ሚሊዮን በላይ የሰራተኛ ሃይል ያስፈልጋል። የዞኑ አርባ … Read moreContinue Reading
- የጎንደርን ከተማ ምን አይነት ተኩስ እንደሌለ ተገለጸ፤ ጎንደር ተይዛለች ተብሎ ነበር“ጎንደር ከተማን ሙሉ በሙሉ ይዘናታል” ሲሉ ስማቸው እንዳይገለጽ ጠይቀው ለጀርመን ድምጽ መረጃ በሰጡ የአማራ ሕዝባዊ ኃይል ፋኖ ቃል አቀባይ አየር ማረፊያውን ሆን ብለው እንዳልያዙ አመልክተዋል። እሳቸው ተናገሩ የተባለው በጀርመን ድምጽ እየተሰማ በለበት ሰዓት በተመሳሳይ የጎንደር ከተማ አስተዳደር ውጊያ መደረጉን ሳያስተባብል ከተማዋን ለመያዝ የገባው ሃይል መደምሰሱን አሃዝ ጠቅሶ አመልክቷል። አገር መከላከያም … Read moreContinue Reading
- “የሞተው ባልሽ ገዳዩ ወንድምሽ፣ሀዘንሽ ቅጥ አጣ ከቤትሽ አልወጣ”የሞተው ባልሽ ገዳዩ ወንድምሽ (ሀዘንሽ ቅጥ አጣ ከቤትሽ አልወጣ) የሚለው የቆየ ተረት ልብን የሚያደማ ኩነትን ማሳያ ነው። እቺ መከረኛ ሚስት ባልዋ በእናቷ ልጅ ወንድሟ ተገደለ። ሟች ባል፣ ገዳይ ወንድም … ኢህአፓ “ሃይማኖት ነው” በሚል ሲገልጸው በነበረው ትግል በቀይና ነጭ ሽብር ስም እናቶች የወላድ መካን ሆነዋል። ጧሪ ያጡና ባዶ ቤት ሃዘን … Read moreContinue Reading