ጆንሰን በቴሌቪዥን ጣቢያው የፕሮግራም አቅራቢ፣ አዘጋጅና ተንታኝ ይሆናሉ። በቀጣይ ዓመት የአሜሪካና የዩኬ ምርጫ በመዘገብ “ቁልፍ ሚና ይጫወታሉ” ተብሏል። “የእንግሊዝን ኃይል የሚያሳይ መሰናዶ” ያቀርባሉም ብሏል ጂኒ ኒውስ። በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዩች ምልከታቸውን ለማጋራት ቃል ገብተዋል።
በዴይሊ ሜይል ላይም አምደኛ የሆኑት ቦሪስ ጆንሰን ሥራቸውን በአውሮፓውያኑ አዲስ ዓመት ይጀምራሉ። ቦሪስ ጆንሰን በኤክስ ገጻቸው ላይ “ጂቢ ኒውስን እንደምቀላቀል ስነግራችሁ በደስታ ነው” ብለው ቪድዮ አጋርተዋል።
“በሩሲያ፣ ቻይና፣ ዩክሬንና ሌሎችም ጉዳዮች እውነተኛ ዕይታዬን አቀርባለሁ” ብለዋል። “እንግሊዝ በዓለም ስላላት ዕምቅ አቅምና ፈተናዎቻችንም እናገራለሁ” ሲሉ አክለዋል። ቦሪስ ከሥልጣን እንዲወርዱ ከፍተኛ ጫና መፈጠሩን ተከትሎ ነው አምና የወረዱት። በኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ወቅት ያሳዩት አመራር አሁንም ምርመራ እየተደረገበት ነው።
በዩኬ የቀድሞ መሪዎች ሥልጣን በለቀቁ በሁለት ዓመታት ስለሚይዙት ሥራ የሚያማክሩት አገራዊ ኮሚቴ አለ። ይህ ኮሚቴ ቦሪስ ጆንሰን ጂቢ ኒውስ መግባታቸው ከመንግሥት መርህ ጋር የሚጻረር ስላልሆነ ፈቅዷል። ሥልጣን ላይ ሳሉ ያገኟቸውን መረጃዎች ያለአግባብ እንዳይጠቀሙ መርሆች ተቀምጠዋል። በተጨማሪም ጂቢ ኒውስን ወክለው መንግሥት ላይ ጫና እንዳያደርጉም ጥንቃቄ ይደረጋል።
ይህ የሚሆነው ሥልጣን ከለቀቁበት ጊዜ በኋላ ላሉት ሁለት ዓመታት ነው። ቦሪስ ከሥልጣን በለቀቁ በአምስት ወራት ውስጥ በተለያዩ መሰናዶዎች ንግግር በማድረግና የግል የሕይወት ታሪካቸውን ለመጻፍ በመስማማት አራት ነጥብ ስምንት ሚሊዮን ፓውንድ አግኝተዋል። ጂቢ ኒውስ ከዚህ በፊት ታዋቂው ኮሜድያን ጆን ክሊስን ቀጥሯል። ጣቢያው ቦሪስ ጆንሰንን ከቀጠረ በኋላ የተመልካቾቹ ቁጥር ከፍ እንደሚል ይጠበቃል።
- “አብይ ባህር ዳር እንዳይመጣ ለማስጠንቀቅ ቦንቦች አፈንድተናል” ፋኖ – አብይ በባህርዳር ድልድይ መረቁበአባይ ወንዝ ላይ የተገነባው የ380 ሜትር ርዝመትና 43 ሜትር ስፋት ያለው ግዙፍ ድልድይ ምረቃ ስነስርዓት ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይና ሌሎችም… Read more: “አብይ ባህር ዳር እንዳይመጣ ለማስጠንቀቅ ቦንቦች አፈንድተናል” ፋኖ – አብይ በባህርዳር ድልድይ መረቁ
- ኢትዮጵያ በአሜሪካ የሚኖሩ “ተፈላጊዎች” ተላልፈው እንዲሰጧት ጥያቄ አቀረበችአሜሪካ ተቀምጠው የኢትዮጵያን ሰላም የሚያውኩ ተፈላጊዎችን ሀገሪቱ አሳልፋ በመስጠት ትብብር እንድታደርግ የፌደራል ፖሊስ መጠየቁ ተገለጸ። በጀርመን በተመሳሳይ ስራ መጀመሩ የሚታወስ… Read more: ኢትዮጵያ በአሜሪካ የሚኖሩ “ተፈላጊዎች” ተላልፈው እንዲሰጧት ጥያቄ አቀረበች
- ሃሰተኛ የተባሉ የዩቲዩበር ባለቤቶች ተያዙ፤ በአንድ ተጠርጣሪ ብቻ ስምንት የዩቲዩብ ቻናል ተከፍቷልፈቃድ ሳይኖራቸው በየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ ስምንት አማረ እና ቤተሰቦቹ በተባለ ህንፃ ላይ ቢሮ ተከራይተው ሃሰተኛና የፈጠራ ወሬ ሲያሰራጩ ነበሩ… Read more: ሃሰተኛ የተባሉ የዩቲዩበር ባለቤቶች ተያዙ፤ በአንድ ተጠርጣሪ ብቻ ስምንት የዩቲዩብ ቻናል ተከፍቷል
- “ከሱዳን ተፋላሚዎች ጀርባ ትህነግ መኖሩን ጌታቸው ረዳ አረጋግጠዋል”፤ የሚለው ዜና የአማራ ፖለቲካን ቀየረበሱዳን ለአንድ ዓመት የዘለቀው የእርስ በእርስ እልቂት ብዙ ተዋንያኖች አሉበት። ከአርቡ ዓለም፣ ከአውሮፓ፣ ከአፍሪቃ፣ ሩሲያና አሜሪካንን ጨምሮ የተለያዩ አካላት የሚዳክሩበት… Read more: “ከሱዳን ተፋላሚዎች ጀርባ ትህነግ መኖሩን ጌታቸው ረዳ አረጋግጠዋል”፤ የሚለው ዜና የአማራ ፖለቲካን ቀየረ
- Are Tigray mercenaries fighting in conflict-ravaged Sudan?Mercenaries from Ethiopia’s Tigray People’s Liberation Front are fighting alongside Sudanese army regulars against fighters of the Rapid Support Forces… Read more: Are Tigray mercenaries fighting in conflict-ravaged Sudan?