የትግራይ ሕዝብ ነሳ አውጪ ግንባር / ትህነግ ” ብቸኛ የአሜሪካና አውሮፓ ጥቅም አስጠባቂ ነኝ፣ የተረጋጋች አገር መምራት የምችለው እኔ ብቻ ነኝ” በሚል የአሚሪካን ፖሊሲ አውጭዎች ለማሳመን በወር ከአንድ ነጥብ አንድ ሚሊዮን ዶላር በላይ ወጪ እንደሚያደርግ ተጠቆመ። ወጪው የነሳ አውጪውን ድርጅት ዓላማ የሚስተጋቡ የሚዲያ ሰዎችና ነጭ አክቲቪስቶች የሚከፈለውን አይተቃልልም።
አምስት ሚሊዮን የሚጠጋ ህዝብ ለምግብ ችግርና አንድ ሚሊዮን የሚሆኑ ዜጎች ለከፋ ችጋር እንደታጋለጡበት የሚነገርለት የትግራይን ክልል ነጻ ለማውጣት የትጥቅ ትግል ላይ የሚገኘው ትህነግ፣ ይህን ያህል ከፍተኛ ሃብት የሚያፈሰው ለስምንት ከወስዋሾች የገዘፉ የህዝብ ግንኙነት የሚሰሩላቸው ድርጅቶች ነው።
በቂ መረጃ እንዳላቸው ጠቅሰው ከኢትዮ 12 ጋር ቃለ ምልልስ ያደረጉት ዶክተር ሓይማኖት እንዳሉት “ትህነጎች ስምንት የህዝብ ግንኙነት የሚሰሩላቸው ድርጅቶ ቀጥረዋል። ከለውጡ በፊት በወር አርባ ሺህ ዶላር ይከፍሏቸው ። ከልወጡ በሁዋላ ከ100 እስከ 140 ሺህ ዶላር እንደሚከፍሏቸው መረጃ አለኝ። ይህን ሁሉ ሃብት እያፈሰሱ ነው ኢትዮጵያ ስሟ እንዳየሳ፣ ጉዳይዋ እንዳይሰማ ሁሉንም በሮች የተቆጣጠሩት። ስልጣን ላይ እየሉ ባከማቹት የዘርፊያ ሃብት የህዝብ ግንኙነቱን ስራ በገንዘብ ቆላልፈው ይዘውታል።”
ለዲሞክራቶች፣ ለሪፐብሊካኖች፣ ለሃይማኖቶች ጥምረት፣ለጥቁር አፍሪካ አሜሪካኖች ጥምረት፣ ለዋይት ሃውስ፣ ለኮንግረንስ፣ Lesbian, Gay, Bisexual and Transgender. q ለሚባሉት ጥምረቶችና ለተቀረው የህብረተሰብ ክፍል በህዝብ ግንኙነት የሚሰሩ የታሰበባቸውና የተመረጡ አቅጣጫዎች መሆናቸውን የስምንቱን ተቋማት ሚና በማስረዳት ዶክተር ሃይማኖት አስረድተዋል። ሙሉ ቃለ ምልልሱን እዚህ ላይ ይመልከቱ። የዚዲዮውን ምልልስ ደግሞ በዩቱብ ቻናላችን እዚህ ላይ ያገኙት።
- ሕገ ወጥ የጦር መሳሪያና የደኅንነት ስጋት – አቅራቢ፣ ፈላጊ፣ ነጋዴ፣ ደላላ ተገናኙና መደበኛ ገበያ ሆነ!በፖለቲካም ሆነ በአካባቢያዊ አጀንዳ ነፍጥ ያነገቡ እና ጦርነትን አማራጭ አድርገው የሚንቀሳቀሱ ኢ -መደበኛ አደረጃጀቶች ሁሉ የጦር መሳሪያ ፍላጎት ይኖራቸዋል፡፡… Read more: ሕገ ወጥ የጦር መሳሪያና የደኅንነት ስጋት – አቅራቢ፣ ፈላጊ፣ ነጋዴ፣ ደላላ ተገናኙና መደበኛ ገበያ ሆነ!
- “የህዝባችንን ድምጽ የሚቀማና የሚያፍን የ’አማራ ስብስብ’ ለአማራ ክልል ተግዳሮት ሆኗል… ትህነግ ዘርፎ እያጋጋዘ ነው” አብን“የትግራይ ተወላጆች ትህነግ ለፈጸመው ወረራ፣ ዘረፋ፣ ማፈናቀልና የግድያ ተግባራት የተቀናጀ የፖለቲካና የሚዲያ ድጋፍ ሰጥተዋል። በተለይም በትግራይ ክልል መቀሌ ከተማ… Read more: “የህዝባችንን ድምጽ የሚቀማና የሚያፍን የ’አማራ ስብስብ’ ለአማራ ክልል ተግዳሮት ሆኗል… ትህነግ ዘርፎ እያጋጋዘ ነው” አብን
- የዜናው ሰም፣ ወርቅና “ትህነግ ብልፅግናን ለመቀላቀል በድርድር ላይ ነው ” የትህነግ ዜናውን አጣጣለለአንድ ቀን ከጮኸና አየሩን ሁሉ ከተቆጣጠረ በሁዋላ ውሃ የተቸለሰበት “ሕወሓት ብልፅግናን ለመቀላቀል በድርድር ላይ ነው” የሚለው የዋዜማ ዜና ፖለቲካውን… Read more: የዜናው ሰም፣ ወርቅና “ትህነግ ብልፅግናን ለመቀላቀል በድርድር ላይ ነው ” የትህነግ ዜናውን አጣጣለ
- የቡድን ሰባት አገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች በኢትዮጵያ ጉዳይ የይሁንታና የስጋት ቅልቅል መግለጫ ሰጡየቡድን ሰባት ሀገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች በተለያዩ ጉዳዮች ላይ መግለጫ ሲሰጡ እግረመንገዳቸውን ኢትዮጵያን አስመልክቶ በበጎ ጎኑንና በስጋት ከፍለው መግለቻቸው… Read more: የቡድን ሰባት አገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች በኢትዮጵያ ጉዳይ የይሁንታና የስጋት ቅልቅል መግለጫ ሰጡ
- ኢዜማ የብርን የመግዛት አቅም ማዳከም የኢኮኖሚውን ስብራት እንደማይጠግን አስታወቀመንግስት ከዓለም ዓቀፉ የገንዘብ ድርጅት ጋር ውይይት ላይ መሆኑ መጠቀሱን ተከትሎ ኢዜማ ” የብርን የመግዛት አቅም ማዳከም የኢትዮጵያን የኢኮኖሚ… Read more: ኢዜማ የብርን የመግዛት አቅም ማዳከም የኢኮኖሚውን ስብራት እንደማይጠግን አስታወቀ