የለንደንን መጠነ-ሥፋት ከ2 እጥፍ በላይ የሚሆን የዓለማችን ትልቁ የበረዶ ግግር ተገምሶ እየሄደ ነው ተባለ፡፡ የበረዶ ግግሩ በፈረንጆቹ 1986 ላይ ከአንታርክቲክ ባሕር ዳርቻ ተቆርሶ በዌድል ባሕር አካባቢ የቆየ ሲሆን፥ ከመጠኑ ግዝፈት አንጻርም ‘የበረዶ ደሴት’ የሚል ስያሜን ይዞ በአካባቢው ከ30 አመታት በላይ ቆይታ አድርጓል። የበረዶ ግግሩ ‘የለንደን’ መጠነ ሥፋት ከሁለት እጥፍ በላይ እንደሚበልጥ ቢቢሲ አስነብቧል፡፡
ከ4 ሺህ ስኩዌር ኪሎ ሜትር በላይ መጠን እና 400 ሜትር መጠነ ውፍረት ያለው የበረዶ ግግር አሁን ላይ በንፋስ እና በመሬት ውስጣዊ ግፊት ከነበረበት ስፍራ ለቆ እየተንቀሳቀሰ መሆኑን ተመራማሪዎች እየገለጹ ነው። አሁን ላይ ግግሩ የአንታርክቲክ ባሕረ ገብ መሬትን ሰሜናዊ ጫፍ እያለፈ መሆኑም ተገልጿል፡፡
ተመራማሪዎች “ኤ23 ኤ” በሚል ሥያሜ የሚያውቁትን የበረዶ ግግር እንቅስቃሴ በቅርበት እየተከታተሉት መሆኑን አስታውቀዋል፡፡
ለበርካታ አመታት በባህር ላይ ሰፍር ዳርቻ የነበረው ግግር እንቅስቅሴ ስጋት እያጫረ መሆኑንም ዘገባው አመላክቷል።
ግግሩ አሁን ከያዘው የጉዞ አቅጣጫ አንጻር በደቡብ ጆርጂያ ዳርቻ ላይ ቢያርፍ በሚሊየኖች የሚቆጠሩ የዓሳ እና የባሕር ወፎች ዝርያዎች የመኖሪያ ምኅዳር እና ብዝኃ-ሕይወት ያቃውሳል የሚል ስጋት አሳድሯል፡፡
በሚፈጠረው አዲስ ያልተለመደ ምኅዳርም በብዝኃ ሕይወቱ ውስጥ አዲስ የሚፈለፈሉት የዓሳ እና ዐዕዋፍት ዝርያዎች አኗኗር ፣ አመጋገብ ፣ አስተዳደግ እና እንቅስቃሴ እንደሚቀየር ከወዲሁ መላ ምት አስቀምጠዋል።
ሌሎች አጥኚዎች ደግሞ እየተገፋ የሚመጣው የበረዶ ግግር ሥጋት ብቻ ሳይሆን ዕድልም ነው ይላሉ፡፡
በውስጡ የተለያዩ ማዕድናት የያዘ እንደመሆኑ የብዝኃ-ሕይወቱ የምግብ ሠንሠለት እንዲቀጥል አስተዋፅዖ አለውም ነው የሚሉት፡፡
ፋና
- “አብይ ባህር ዳር እንዳይመጣ ለማስጠንቀቅ ቦንቦች አፈንድተናል” ፋኖ – አብይ በባህርዳር ድልድይ መረቁበአባይ ወንዝ ላይ የተገነባው የ380 ሜትር ርዝመትና 43 ሜትር ስፋት ያለው ግዙፍ ድልድይ ምረቃ ስነስርዓት ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይና ሌሎችም ታዳሚዎች እንዳይገኙ ፋኖ በተመረጡ… Read more: “አብይ ባህር ዳር እንዳይመጣ ለማስጠንቀቅ ቦንቦች አፈንድተናል” ፋኖ – አብይ በባህርዳር ድልድይ መረቁ
- ኢትዮጵያ በአሜሪካ የሚኖሩ “ተፈላጊዎች” ተላልፈው እንዲሰጧት ጥያቄ አቀረበችአሜሪካ ተቀምጠው የኢትዮጵያን ሰላም የሚያውኩ ተፈላጊዎችን ሀገሪቱ አሳልፋ በመስጠት ትብብር እንድታደርግ የፌደራል ፖሊስ መጠየቁ ተገለጸ። በጀርመን በተመሳሳይ ስራ መጀመሩ የሚታወስ ነው። ኢትዮጵያ በአሜሪካ የሚኖሩ… Read more: ኢትዮጵያ በአሜሪካ የሚኖሩ “ተፈላጊዎች” ተላልፈው እንዲሰጧት ጥያቄ አቀረበች
- ሃሰተኛ የተባሉ የዩቲዩበር ባለቤቶች ተያዙ፤ በአንድ ተጠርጣሪ ብቻ ስምንት የዩቲዩብ ቻናል ተከፍቷልፈቃድ ሳይኖራቸው በየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ ስምንት አማረ እና ቤተሰቦቹ በተባለ ህንፃ ላይ ቢሮ ተከራይተው ሃሰተኛና የፈጠራ ወሬ ሲያሰራጩ ነበሩ የተባሉ ተጠርጣሪዎች መያዛቸው ተገለጸ።… Read more: ሃሰተኛ የተባሉ የዩቲዩበር ባለቤቶች ተያዙ፤ በአንድ ተጠርጣሪ ብቻ ስምንት የዩቲዩብ ቻናል ተከፍቷል
- “ከሱዳን ተፋላሚዎች ጀርባ ትህነግ መኖሩን ጌታቸው ረዳ አረጋግጠዋል”፤ የሚለው ዜና የአማራ ፖለቲካን ቀየረበሱዳን ለአንድ ዓመት የዘለቀው የእርስ በእርስ እልቂት ብዙ ተዋንያኖች አሉበት። ከአርቡ ዓለም፣ ከአውሮፓ፣ ከአፍሪቃ፣ ሩሲያና አሜሪካንን ጨምሮ የተለያዩ አካላት የሚዳክሩበት በዚህ ጦርነት የትግራይ ህዝብ… Read more: “ከሱዳን ተፋላሚዎች ጀርባ ትህነግ መኖሩን ጌታቸው ረዳ አረጋግጠዋል”፤ የሚለው ዜና የአማራ ፖለቲካን ቀየረ
- Are Tigray mercenaries fighting in conflict-ravaged Sudan?Mercenaries from Ethiopia’s Tigray People’s Liberation Front are fighting alongside Sudanese army regulars against fighters of the Rapid Support Forces (RSF), the paramilitary group… Read more: Are Tigray mercenaries fighting in conflict-ravaged Sudan?