በሰሜን ወሎ ዞን ላልይበላ ከተማ የሚገኘው የቅዱስ ላልይበላ ጠቅላላ ሆስፒታል በከተማዋ ለአራት ወራት ያህል ከርሞ የነበረውን የሽብር ቡድኑን የጭካኔ በትር ተጋፍጦ አገልግሎቱ ሲሰጥ መቆየቱን የሆስፒታሉ ተወካይ ሥራ አስኪያጅ አስታወቁ።
ግፈኛውና አሸባሪው ቡድን የሆስፒታሉን ባለሙያዎች ከመደብደብ አልፎ የሆስፒታሉን ቁሳቁስ በመዝረፍ እና በመሰባበር የክፋቱን ጥግ አሳይቷል ብለዋል።
ሆስፒታሉን በተወካይ ሥራ አስኪያጅነት እየመሩ የሚገኙት ባዮ ሜዲካል ኢንጂነር ሲሳይ ታመነ በተለይ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንዳስታወቁት፤ ሆስፒታሉ በአካባቢው ላሉ 300 ሺ የኅብረተሰብ ክፍል አገልግሎት የሚሰጥ ነው። ወራሪው ኃይል ወደ ላልይበላ ከተማ ከገባ ጀምሮ ለአንድ ሁለት ቀን ያህል ሥራ አቋርጦ የነበረ ቢሆንም ወዲያው ኮሚቴ ተዋቅሮ የሽብር ቡድኑን የግፍ በትር በመቋቋም በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ወደሥራ ገብቷል።
በሆስፒታሉ የተቋቋመው ኮሚቴ፣ ለጊዜው የተወሰኑ ዲፓርትመንቶችን በማጠፍ በተለይ ወላጆችንና ስር የሰደደ (ክሮኒክ) ችግር ያለባቸውን ህሙማን አሸባሪው ኃይል የሚያደርሰውን ፈተና በመጋፈጥ ሲያገለግሉ መቆየታውን ተወካይ ሥራ አስኪያጁ አስረድተዋል።
እርሳቸው እንዳሉት፤ የሆስፒታሉ ባለሙያዎች መንገድ ላይ እየተደበደቡም ቢሆን ወራሪው ኃይል ከተማውን ተቆጣጥሮት በቆየባቸው በአራት ወር ውስጥ ወደ 34 እናቶች በኦፕራሲዮን እንዲወልዱ ማድረግ ችለዋል። ከአምስት ሺ በላይ የሆኑ ስር የሰደደ በሽታ ያለባቸው ታማሚዎች ወደ ሆስፒታሉ መጥተው ተስተናግደዋል። በዚህ አስቸጋሪ ጊዜ ውስጥ ስራውን ሳያቋርጥ ቆይቷል።
በወራሪው ኃይል ተደፍረው ከመጡ ሴቶች መካከል ሁለት ታካሚዎች ሲሆኑ፣ አንዷ እመጫት መሆኗን የተናገሩት ተወካዩ፣ በኑሮ ደረጃዋም ዝቅተኛ ከሚባሉት መካከል የምትመደብ መሆኗ ተናግረዋል። ተደፍረው የመጡ ሴቶች በተገቢው መንገድ አገልግሎት እንደተሰጣቸውም አመላክተዋል።
በሆስፒታሉ የተቋቋመው ኮሚቴ ሰብሳቢ የሆኑት አቶ አቤኔዘር ፈንቴ በበኩላቸው፤ ሆስፒታሉ በከባድ ፈተና ውስጥ ሆኖ ሲሰራ የቆየ ነው ብለዋል። በተለይ የሆስፒታሉ የፋርማሲ ባለሙያዎች ይደበደቡ እንደነበርም ተናግረዋል። በዚህ ሁሉ ውስጥ የሆስፒታሉ ባለሙያዎች የወራሪውን ዱላ ሳይፈሩ ተቋቁመው አገልግሎት ሲሰጡ መቆየታቸውን ገልጸዋል።
እንደ ኮሚቴ ሰብሳቢው ገለጻ፤ አንዲት እናት ልትወልድ ወደሆስፒታሉ መጥታ እርሷን ለማዋለድ በሚደረገው ሂደት ለጄኔሬተር ናፍጣ መጠቀም እየተፈለገ ወራሪው ኃይል ግን ናፍጣውን በጉልበት ይወስድ ነበር። ከሆስፒታሉ አውቶቡሶች ውስጥ ሁሉ ናፍጣውን በቱቦ እየሳበ ይጠቀም ነበር።
ሆስፒታሉ ከዚህ በኋላ በርካታ ወረዳዎችን የሚያገለግል እንደመሆኑ የክልል ጤና ቢሮ የተለየ ትኩረት ሊሰጠው ይገባል ሲሉ አቶ አቤኔዘር ጥሪ አስተላልፈዋል። ሆስፒታሉ በመከራ ውስጥ ሆኖ አገልግሎት ሲሰራ በተመቻቸ ሁኔታ አለመሆኑም መታወቅ አለበት ብለዋል።
በሆስፒታሉ የሐብት አፈላላጊ ኮሚቴ አባል የሆኑት አቶ መለሰ አሰፋ በበኩላቸው፤ ወራሪው ኃይል ሆስፒታሉን ካምፕ አድርጎ መክረሙን ተናግረዋል። በዚህም የተነሳ ሆስፒታሉ ለአንድ ሁለት ቀን አገልግሎት መስጠት ያቆመ መሆኑን ጠቅሰው፤ ኮሚቴ ተዋቅሮ ከሁለት ቀን በኋላ ወደ ሆስፒታሉ ሲገባ ምንም አይነት መድኃኒት እንዳልነበር ገልጸዋል። በዚህም የተነሳ የላስታ ላልይበላ ተወላጆች አስቸኳይ እርዳታ በማቋቋም መድኃኒት ተገዝቶ ከዞኑ መቄት ከሚባል ወረዳ ከፍላቂት ከተማ መድኃኒት ተገዝቶ በአህያ ተጭኖ መምጣቱን አስታውሰዋል።
በዚህ መሃል ግን ስር የሰደደ በሽታ ያለባቸው ታማሚዎች ይሞቱ እንደነበር አስታውሰዋል። የቅዱስ ላልይበላ ሆስፒታል ክፍት ነው በሚልም ከወልዲያ፣ ከቆቦና ላስታ ድረስ ሰዎች መጥተው ይታከሙ እንደነበር አመልክተዋል።
አቶ መለስ፣ እንዳሉት፣ በወቅቱ ወደ13 የስራ ክፍሎች በወራሪው ኃይል ተሰባብረዋል። ማህበረሰቡን ሲያገለግሉ የነበረው የጥገና ስራ በማካሄድ ነው። በርካታ የሆስፒታሉ እቃዎች በሽብር ቡድኑ አባላት ተሰርቀዋል። በተለይ የህክምና አላቂና ቋሚ እቃዎች ተወስደዋል።
አስቴር ኤልያስ አዲስ ዘመን ታህሳስ 20 ቀን 2014 ዓ.ም
- ሕገ ወጥ የጦር መሳሪያና የደኅንነት ስጋት – አቅራቢ፣ ፈላጊ፣ ነጋዴ፣ ደላላ ተገናኙና መደበኛ ገበያ ሆነ!በፖለቲካም ሆነ በአካባቢያዊ አጀንዳ ነፍጥ ያነገቡ እና ጦርነትን አማራጭ አድርገው የሚንቀሳቀሱ ኢ -መደበኛ አደረጃጀቶች… Read more: ሕገ ወጥ የጦር መሳሪያና የደኅንነት ስጋት – አቅራቢ፣ ፈላጊ፣ ነጋዴ፣ ደላላ ተገናኙና መደበኛ ገበያ ሆነ!
- ምን ያክል ተዘጋጅተናል? ጥድፊያ አገር አልባ ለመሆን !! ህጻናቱ ምን አጠፉ?ያለፈውን ግማሽ ምዕተ ዓመት የኢትዮጵያ ፖለቲካ እና ሥነ መንግሥት ታሪክ በጥሞና የተከታተለ ኢትዮጵያዊ የግዛት… Read more: ምን ያክል ተዘጋጅተናል? ጥድፊያ አገር አልባ ለመሆን !! ህጻናቱ ምን አጠፉ?
- የደም ግፊት በመለካትና ክትትል በማድረግ የስትሮክ ተጋላጭነትን መቀነስአንድ ሰው የደም ግፊት መጠኑ ከፍተኛ ከሆነ እና በጊዜው ሕክምና ካላደረገ ለከፍተኛ የልብ በሽታና… Read more: የደም ግፊት በመለካትና ክትትል በማድረግ የስትሮክ ተጋላጭነትን መቀነስ
- የስኳር ህመም አይነቶች እና ምልክቶችየስኳር ህመም በደም ውስጥ የስኳር መጠን ከሚገባው በላይ ሆኖ በሚገኝበት ሰዓት የሚከሰት ተላላፊ ያልሆነ… Read more: የስኳር ህመም አይነቶች እና ምልክቶች
- ማንኮራፋትና ትዳርን እስከ ማፍረስ የሚያደርሰው መዘዙ ? ማንኮራፋት መፍትሄ አለው?የማንኮራፍት መዘዙ እንቅልፍ ማሳጣት ብቻ አይደለም። ማንኮራፋት ከሚያንኮራፉት ሰዎች ጎን በሚተኙ ሰዎች አካላዊ እና… Read more: ማንኮራፋትና ትዳርን እስከ ማፍረስ የሚያደርሰው መዘዙ ? ማንኮራፋት መፍትሄ አለው?
- Ethiopia Working To Secure New Development Bank MembershipThe Ministry of Foreign Affairs disclosed that Ethiopia is working hard to become member… Read more: Ethiopia Working To Secure New Development Bank Membership
- የትግራይ ክልል ታጣቂዎች ዳግም ዝርፊያ እያፈጸሙ ነው፤ የተማሪዎች መጽሃፍትን “የአማራ ክልል ናቸው እየሉ ቀደዋል”በአላማጣ ከተማ በተለየ መልኩ የትግራይ ክልል ታጣቂዎች በከተማዋ ውስጥ እንደሚንቀሳቀሱ ነዋሪዎች መመስከራቸውን ቢቢሲ አስታወቀ።… Read more: የትግራይ ክልል ታጣቂዎች ዳግም ዝርፊያ እያፈጸሙ ነው፤ የተማሪዎች መጽሃፍትን “የአማራ ክልል ናቸው እየሉ ቀደዋል”
- በዘንድሮው ዓመት የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ኢትዮጵያ ሰባት ነጥብ ሁለት ቢሊዮን ችግኝ ልትተክል ነውለዘንድሮ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር 6 ነጥብ 5 ቢሊየን ችግኝ ለመትከል ዕቅድ መያዙንna ለዚህም ተግባራዊነት… Read more: በዘንድሮው ዓመት የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ኢትዮጵያ ሰባት ነጥብ ሁለት ቢሊዮን ችግኝ ልትተክል ነው
- አፍሪካ ህብረት ” የውጭ ምንዛሪ ሒሳቡን ወደ ሌላ ሀገር ሊያዘዋውር ነው” የሚለው ዜና ሃሰት መሆኑን አረጋገጠአፍሪካ ህብረት የውጭ ምንዛሬ አካውንቱን ወደ ሌላ አገር እንደሚያዘዋውር ተጠቅሶ በህብረቱ ስም የወጣው ዜና… Read more: አፍሪካ ህብረት ” የውጭ ምንዛሪ ሒሳቡን ወደ ሌላ ሀገር ሊያዘዋውር ነው” የሚለው ዜና ሃሰት መሆኑን አረጋገጠ
- አፍሪቃ ህብረት ምን አሰጋውና “ገንዘቤን ወደ ሌላ አገር ለማዛወር እያሰብኩ ነው” ሲል ተንሿከከ፤ የጾምና የፍስክ ዜናዎችባንኩ የክፍያ ሰነድ ቀረበለት። ማጣሪያ ጥያቄ ለህብረቱ አቀረበ። ሃሰት ሆኖ ተገኘና ፖሊስ ተጠርጣሪዎቹን ያዘ።… Read more: አፍሪቃ ህብረት ምን አሰጋውና “ገንዘቤን ወደ ሌላ አገር ለማዛወር እያሰብኩ ነው” ሲል ተንሿከከ፤ የጾምና የፍስክ ዜናዎች
- የኢትዮጵያ ኤልክትሪክ ኃይል 300 ቢሊዮን ብር የንግድ ባንክ ዕዳ አለብኝ አለ፤ ዕዳውና የክፍያው ጫና እንደከበደውም አስታውቋልየኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከንግድ ባንክ 300 ቢሊዮን ብር ዕዳ እንዳለበት ተገለጸ። የዕዳ ጫናውን ለማቃለል… Read more: የኢትዮጵያ ኤልክትሪክ ኃይል 300 ቢሊዮን ብር የንግድ ባንክ ዕዳ አለብኝ አለ፤ ዕዳውና የክፍያው ጫና እንደከበደውም አስታውቋል