በእንግሊዝ እየተካሄደ ያለው የቡድን 7 ሃገራት ስብስባ ዛሬ መግለጫ አውጥቷል:: በመግለጫው የኢትዮጵያ ጉዳይም ተካቷል:: በአንቀፅ 54 ላይ የሰፈረው መግለጭ ቃል በቃል የሚከተለውን ይላል።
ትርጉም
54. “በኢትዮጵያ ትግራይ ክልል ውስጥ እየተካሄደ ባለው ግጭት እና እየወጡ ባሉ ሪፖርቶች ምናልባት በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች በረሃብ ሁኔታ ውስጥ ሊሆኑ ስለሚችሉ የሰብአዊ አደጋዎች በጣም ያሳስበናል፡፡ የጾታ ጥቃትን ጨምሮ እየተፈፀሙ ያሉ አሰቃቂ ድርጊቶችን እናወግዛለን ፣ የተባበሩት መንግስታት የሰብዓዊ መብቶች ከፍተኛ ኮሚሽን (OHCHR) ምርመራዎችንም በደስታ እንቀበላለን እንዲሁም በትግራይ ለተፈጸሙ የሰብአዊ መብት ጥሰቶች ሙሉ ተጠያቂነት እንዲሆኑና ወንጀለኞቹም ለህግ እንዲቀርቡ እንጠይቃለን፡፡ ግጭት በፍጥነት እንዲቆም ፣ ያልተዳረሰ ሰብዓዊ አቅርቦት ወደ ሁሉም አካባቢዎች እንዲደርስ እና የኤርትራ ኃይሎች በፍጥነት እንዲወጡ እንጠይቃለን፡፡ ለችግሩ ብቸኛ መፍትሄ ተአማኒ የፖለቲካ ሂደት ሁሉም ወገኖች እንዲከተሉ እንጠይቃለን፡፡ በቀጣይም የኢትዮጵያ መሪዎች የሰብአዊና የፖለቲካ መብቶችን በማክበር ላይ በመመስረት ብሄራዊ እርቅ እና መግባባት እንዲፈጠር ሰፋ ያለ ሁሉን አቀፍ የፖለቲካ ሂደት እንዲያራምዱ ጥሪ እናቀርባለን፡፡” ትርጉሙ የተወሰደው ከደጀኔ አሰፋ ነው።
በዚህ አንቀጽ መሰረት ኢትዮጵያ ያልተስማማቸው ከትህነግ ጋር ንግግር የሚባለውን ህሳብ ነው። አልተካተተም። ጥቅል የፖለቲካ ፈውስ እንደሚያስፈልግ መንግስትም አምኗል። አስቀድሞ ተናግሯል። የሚገባ ምክር ነው ተብሏል። አሜሪካ ያወጣቸው መግለጫ ሲጨመቅ አይነት ነውልል
- ከሱዳን ተፋላሚዎች ጀርባ ትህነግ መኖሩን ጌታቸው ረዳ አረጋገጡ፤ በትግራይ አስተዳደር ስም ማስተባበያም አውጥተዋልበሱዳን ለአንድ ዓመት የዘለቀው የእርስ በእርስ እልቂት ብዙ ተዋንያኖች አሉበት። ከአርቡ ዓለም፣ ከአውሮፓ፣ ከአፍሪቃ፣ ሩሲያና አሜሪካንን ጨምሮ የተለያዩ አካላት… Read more: ከሱዳን ተፋላሚዎች ጀርባ ትህነግ መኖሩን ጌታቸው ረዳ አረጋገጡ፤ በትግራይ አስተዳደር ስም ማስተባበያም አውጥተዋል
- Are Tigray mercenaries fighting in conflict-ravaged Sudan?Mercenaries from Ethiopia’s Tigray People’s Liberation Front are fighting alongside Sudanese army regulars against fighters of the Rapid Support… Read more: Are Tigray mercenaries fighting in conflict-ravaged Sudan?
- Sudan’s RSF Accuse Tigray People’s Liberation Front of Backing SAFSudanese warring party Rapid Support Forces has officially accused the Tigray People’s Liberation Front Fighters of fighting in Sudan… Read more: Sudan’s RSF Accuse Tigray People’s Liberation Front of Backing SAF
- የኢትዮጵያን – “መከራዋን ካልተሸከምንላት ኢትዮጵያዊነቱ ምኑ ላይ ነው” አብይ አሕመድ“ኢትዮጵያ ኢትዮጵያ” እያሉ በስሟ ሲምሉ የነበሩ ብዙዎች ነበሩ፤ ከልባቸው ለቃላቸው ታምነው ልጅ የሆኗት ግን ጥቂቶች ብቻ ናቸው። አንዳንዶች በስሟ… Read more: የኢትዮጵያን – “መከራዋን ካልተሸከምንላት ኢትዮጵያዊነቱ ምኑ ላይ ነው” አብይ አሕመድ
- አቡነ አብርሃም “እንዳይረፍድብን” ሲሉ ለመጸጸት እንኳን ዕድል እንዳይታጣ አስጠነቀቁ“ወገኖቼ እንማርና እናስተምር፣ ወንጀልን እንጸየፈው፣ እንጥላው፣ ወንጀልን ተጸይፈን ወንጌልን እንውደደው፣ በወንጌል እንኑር፣ ወንጌል ሕጓም ስርዓቷም ያማረች ናት፤ ወንጌላዊ መኾን… Read more: አቡነ አብርሃም “እንዳይረፍድብን” ሲሉ ለመጸጸት እንኳን ዕድል እንዳይታጣ አስጠነቀቁ