የእስራኤልና የፍልስጤሙ ሃማስ ጦርነት ዛሬም መቀጠሉ ተነግሯል።ጦርነቱ ሰፍቶ ሌሎች ኃይሎችም እንዳይጨመሩ ስጋቶች ከቀን ወደ ቀን እያየሉ ነው።
✔️- እስራኤል የሰብዓዊ እርዳታ በግብፅ እና ጋዛ ድንበር በኩል ወደ ጋዛ ሰርጥ እንዲገባ ፈቅዳለች ተብሎ በተለያዩ ሚዲያዎች ቢዘገብም የእስራኤል ጦር ” የተኩስ አቁም የሚባል ነገር የለም ፤ መሻገሪያዎቹም እንደተዘጉ ናቸው ከወንጀለኛው ሃማስ ጋር መዋጋታችንን እና ማጥቃታችንን እንቀጥላለን። ጋዛ የትግላችን ማዕከል ናት የታገቱ እስራኤላውያንን ይዛለች ” ብሏል።
✔️- ” ሃማስ የፍልጤምን ህዝብ አይወክልም ” ያሉት የፍልስጤሙ ፕሬዜዳንት ማሃሙድ አባስ ” በሁለቱም በኩል በሲቪል ሰዎች ላይ የሚፈፀመውን ግድያ እቃወማለሁ ፤ በሁለቱም በኩል የታገቱ እና የታሰሩ እስረኞች ሊለቀቁ ይገባል ” ብለዋል።
✔️- ኢራን በጋዛ ውስጥ ላለው ጦርነት የፖለቲካ መፍትሄዎች የሚያገኝበት ጊዜ እያለቀ ነው ስትል አስጠንቅቃለች። ኢራን የጦርነቱ መስፋፋት ወደማይቀርበት ደረጃ መቃረቡን አመልክታለች።
✔️- የእስራኤል ጠ/ሚ ቤኒያሚን ኔታንያሁ ፤ ” ግባችን ድል ማድረግና እና ሀማስን ማስወገድ ነው ” ብለዋል። ” ኢራንን እና ለሂዝቦላህን ተጠንቀቁ ” ብለዋቸዋል። ” ለቤተሰቦቻችን ግዴታ አለብን ” ያሉት ኔታንያሁ ” የታገቱትን ሰዎችን እስክንመልስ ድረስ አንታክትም።” ብለዋል።
✔️- ሃማስ ያገታቸውን ሰዎች ለመልቀቅ እስራኤል ውስጥ የታሰሩ 6000 እስረኞች እንዲለቀቁ መጠየቁ ተዘግቧል። ሃማስ አሁን ላይ ከ200 – 250 የሚደርሱ ታጋቾችን መያዙን አመልክቷል። 22 የእስራኤል ታጋቾች በእስራኤል የአየር ጥቃት ተገድለዋል ሲል ገልጿል።
✔️- የአሜሪካው የመከላከያ ሚኒስትር ሎይድ ኦስቲን ለተወሰኑ የአሜሪካ ወታደሮች እስራኤል በምትፈልጋቸው ጊዜ ” ለመሰማራት ዝግጁ ሁኑ ” የሚል ትዕዛዝ መስጠታቸውን ፎክስ ኒውስ አንድ ስማቸው ያልተገለፀ ባለስልጣንን ዋቢ አድርጎ ዘግቧል። ዎል ስትሪት ጆርናል እንደዘገበው ወደ 2,000 የሚጠጉ የአሜሪካ ወታደሮች ተመርጠዋል ፤ ነገር ግን ይህ ቁጥር አልተረጋገጠም ተብሏል።(BirlikEthiopia)
- ሰው ሰራሽ ቦይ በመገንባት ቀይ ባህርን መቀላቀል የኢትዮጵያ ሌላ አማራጭ?አርተፊሻል ቦይ በመገንባት ቀይ ባህርን ወደ ኢትዮጵያ በማምጣት ኢትዮጵያ የባህር በር ሊኖራት ይችላል፤ ይህ በአለም ላይ በኢትዮጵያ የአፋር ምድር ረባዳነት የተነሳ ተፈጥሮ የሰጠው እድል ነው! በኢትዮጵያ እና በኤርትራ መካከል አርተፊሻል ቦይ በመስራት ኢትዮጵያ የወደብ ባለቤት መሆን ትችላለች፡፡ እንደዚህ አይነት አጋጣሚ ሊፈጠር የቻለው፤ የኢትዮጵያ የአፋር ቦታ ከባህር ወለል በታች እስከ 110 … Read moreContinue Reading
- ብሄራዊ ባንክ የገንዘብ ቁጥጥሩን አጠንክሮ እንደሚገፋበት አስታወቀ፤ ህገወጥ የወርቅ አዘዋዋሪዎች ላይ እርምጃ እየተወሰደ ነው– የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ አዲስ የማቋቋሚያ ረቂቅ አዋጅ አዘጋጀ በአገሪቱ የሚታየውን የዋጋ አለመረጋጋት ለመግራት የግንዘብ ስርጭት ላይ ጥብቅ ቁጥጥር በማድረግ የተጀመረው ስራ ውጤት እያሳየ መሆኑ ተመለከተ፤ ተጠናክሮ ክምሩ እንደሚሰራበትና ግሽበትን በዓመቱ መጨረሻ 20 ከመቶ ለማድረስ መታቀዱ ተሰማ። ህገወጥ የወርቅ ነጋዴዎች ላይ ጥብቅ ቁጥጥርና የማበረታቻ መደረጉ ለውጥ ቢያሳይም በቂ እንዳልሆነ ተመለከተ። … Read moreContinue Reading
- የኮሚሽኑ የቀድሞ ሠራተኞች ከ40 ሚሊየን ብር በላይ የሙስና ክስ ጋር ተያይዞ ያቀረቡት የክስ መቃወሚያ ውድቅ ሆነየአዲስ አበባ እሳት እና አደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን የቀድሞ ሠራተኞች ከ40 ሚሊየን ብር በላይ የአልባሳት ግዢ ጋር ተያይዞ በቀረበባቸው የሙስና ወንጀል ክስ ያቀረቡት የክስ መቃወሚያ ውድቅ ተደረገ። ተከሳሾቹ ያቀረቡትን የክስ መቃወሚያ ውድቅ ያደረገው የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 3ኛ የሙስና ጉዳዮች ወንጀል ችሎት ነው። የፍትሕ ሚኒስቴር የሙስና ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ዐቃቤ … Read moreContinue Reading
- መንግስት የነዳጅ ድጎማን በህገወጥ መንገድ ሲጠቀሙ ነበሩ ያላቸውን 40 ሺህ ተሽከርካሪዎች ከስርአቱ አስወጣ፣ የሰርቁትን ይከፍላሉየታለመለት የነዳጅ ድጎማን ላልተገባ ዓላማ ሲጠቀሙ የነበሩ 40 ሺህ ተሽከርካሪዎች ከድጎማ ስርዓቱ እንዲወጡና ዕዳ እንዲከፍሉ መደረጉን የፕላንና ልማት ሚኒስትር ዶክተር ፍጹም አሰፋ ገለጹ። ሚኒስትሯ ይህን ያሉት የመንግሥት የ2016 የመጀመሪያ የሩብ ዓመት አፈጻጸም በተገመገመበት ወቅት ነው። የግምገማው ተሳታፊዎች መንግሥት የነዳጅ ድጎማን ጨምሮ በርካታ የህዝብ ተጠቃሚነትን የሚያረጋገጡ ተግባራትን ማከናወኑን አድንቀው፤ ሆኖም” ድጎማው … Read moreContinue Reading
- በዓመት አምስት ሚሊዮን ቶን ሲሚንቶ የሚያመርተው ፋብሪካ ከመጋቢት በሁዋላ የሲሚንቶ ዋጋ ወደ ነበረበት የሚመልሰ ነውበቀን 10 ሺህ ቶን ሲሚንቶ እንዲያመርት እቅድ ተይዞለት በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን እንሳሮ ወረዳ ለሚ ከተማ እየተገነባ ያለውን የለሚ ናሽናል ሲሚንቶ ፋብሪካ የግንባታ በመጋቢት ወር ይጠናቀቃል። ምርቱ በተባለው ወር ሲጀምር የሲሚንቶ ዋጋ አሁን ካለበት በግማሽ እንደሚወርድ ይጠበቃል። ከመጋቢት በሁዋላ ፋብሪካው በ50 በመቶ የሲሚንቶ እጥረቱን ያስወግዳል። ኢስት አፍሪካን ሆልዲንግ ኩባንያ … Read moreContinue Reading