ከ92 ዓመታት በፊት ጥቅምት 5 ቀን 1924 ዓ.ም የሀገራችን ብርቅዬ ሁለገብ የጥበብ ሰው ሠዓሊና ባለቅኔ ገብረክርስቶስ ደስታ የተወለደበት ቀን ነው።
በኢትዮጵያ ዘመናዊ የስነ ጥበብ ታሪክ ውስጥ ጉልህ ስፍራ የነበረው ሠዓሊና ባለቅኔ ገብረክርስቶስ ደስታ በኢትዮጵያ ዘመናዊ የስነጥበብ ህዋ ላይ በተለይም አብስትራክት የተሰኘውን እና ዘመናዊ የስዕል አሰራር ስልት በስፋት ከማስተዋወቅ በላይ የራሱ የሆነ የአሳሳል ጥበብ በመጠቀም በሚስላቸው ስዕሎቹ የሀገራችንን ማህበረሰብ ህይዎት በአመዛኙ በመግለጽ የጥበብና የዜግነት ግዴታውን በመስዋእትነት ጭምር የተወጣ የሀገራችን ታላቅ የጥበብ ሰው ነበር።
ሰዓሊ ገብረ ክርስቶስ ደስታ ስዕል በሚያስተምርበት ወቅት ተማሪዎቹ የኢየሱስ ክርስቶስን ስዕል ስለዉ እንዲያመጡ በቤት ስራ መልክ አዘዛቸው። ሁሉም በመሠለዉ መልክ ኢየሱስን ስሎ ሲያመጣ አንድ ተማሪ ግን የክርስቶስን ስዕል በጥቁር ወይም አፍሪካዊ መልክ ስሎ ያስረክባል። ገብረ ክርስቶስ በስእሉ ተገርሞ ለምን ክርስቶስን ጥቁር አድርጎ እንደሳለው ሲጠይቀው ተማሪው «ክርስቶስ ፈረንጅ ሊሆን አይችልም ምክንያቱም ፈረንጆች በጣም ጨካኞች ናቸው። ኢየሱስ ነጭ ሳይሆን ጥቁር ነው» ብሎ ይመልሳል። ይሄን ጊዜ ነው ሰአሊው ገብርዬ ወደቤቱ ሲበር ሄዶ ኢየሱስ ክርስቶስን ቀለም እንዳይኖረው ፣ ዘር እንዳይኖረው ፣ ነገድ እንዳይኖረው አርጎ ከፀጉሩ እስከእግር ጥፍሩ ድረስ በደም ለውሶ ሳለው። በስእሉም ፍቅር ዘር የለውም። ፍቅር ቀለም የለውም። ፍቅር የነገድና የቀለም አጥርን ይሻገራል። ክርስቶስ ሲያድነን ዘር ቀለም ፆታ አልመረጠም። በማለት ለትውልድ አስቀምጦ ሄዷል።
እንደ ዘመናዊ ስዕሎቹ ሁሉ በኢትዮጵያ የስነ ግጥም ባህልም ውስጥ ገብረ ክርስቶስ እንደ አዲስ ዘመናዊ ግጥም ከፍ ያደረገም ነበር። አዳዲስ የግጥም ዘዴ በመከተል በኢትዮጵያ የስነ ግጥም ባህል ውስጥ አዲስ ንቅናቄ የፈጠሩ ግጥሞቹና ቅኔዎቹ የአማረኛ ቋንቋን ጣዕምና ለዛ ግልጽና ቀላል በሆነ ፤ ነገር ግን ቅኔያዊ ውበትን በተጎናጸፈው የገለጻ ሀይል እስከ ባህላዊ ትውፊታችንን ተሻግረው የኢትዮጵያዊያንን ነፍስ የገለፁ ናቸው።
የሀገራችንን መልካምድራዊ ገጽታ ከመቅረታቸውም በላይ ለአገሩ ባህለኛነቱን እና ወገን ወዳድነቱን በአጠቃላይ ኢትዮጵያዊ ስብዕናውን አሟልተው የገለጹለት ናቸው።
ከነበሩን ብርቅዬ የጥበብ ሰዎች አንዱ ሁለገቡ የጥበብ ሰው በዘመነ ደርግ በህይወቱ ላይ ባንዣበበ አደጋ በመስከረም ወር 1971 ሀገሩን በስደት ጥሎ እንደወጣ ቀረ ከተሰደደ ከዓመታት እንግልት በኋላ መጋቢት 21 ቀን 1973 ዓ.ም በተወለደ በ 49 ዓመቱ አሜሪካ ኦክላሆማ ግዛት ህይዎቱ አለፈች ፡ በወቅቱ አስክሬኑ ጭምር ሀገር የከዳ ተብሎ ለአገሩ መሬት ሳይታደል ግብአተ መሬቱም እዚያው ተፈጸመ።
ይሄን የህይዎቱን ትራጂዲያዊ ፍፃሜ አስመልክቶ ዛሬ በህይዎት የለሉትና ተቆርቋሪ የስነጥበብ የታሪክ ምሁር ስዩም ወልዴ የሰአሊ ገብረ ክርስቶስ ደስታ ግጥሞች 1981 በሚለው ዝክረ ጽሑፋቸው እንዲህ ደምድመውታል። “የገብረክርስቶስ ሞት ተራ የአካል ሞት ነው። ይሁን እንጂ ሞቱን ትራጂዳዊ የሚያደረገው አንድ ቁም ነገር በግጥሞቹ ውስጥ እናገኛለን። በተለያዩ ግጥሞቹ ውስጥ ተመልስ እስኪረግጣት የሚናፍቃት እኔም ከእናንተ የምትበልጥ ሀገር አለችኝ የሚላት ፤ሰው ከሀገሩ ውጭ ሰው አይደለም ብሎ ሲተማመንባት የነበረች ሀገሩ ፣ የህይወቱን የመጨረሻ ህልፈት ሳታስተናግድለት መቅረቷ ነው”።
እንኳን ሞቶ አስከሬኑን ይቅርና ቅፅበታዊ ትንፋሹን እንኳን በባዕድ ሀገር መተንፈስ የማይፈልገው ገብረክርስቶስ በ1973 በኦክላሆማ እስቴት ማረፉ ለሀገር ወዳዱ ድንቅ ባለውለታችን የህይወት መጨረሻ የሚያስታውስ አሳዛኝ ክስተት ነው።
ክብር ለሚገባቸው ክብር ሰጥተን ልንዘክራቸው በዘመን ኮርቻ ወደኃላ እንሳፈራለን | መናኻሪያ ኤፍኤም 99.1
ዓብዱራሕማን ጋሻው
- ሰው ሰራሽ ቦይ በመገንባት ቀይ ባህርን መቀላቀል የኢትዮጵያ ሌላ አማራጭ?አርተፊሻል ቦይ በመገንባት ቀይ ባህርን ወደ ኢትዮጵያ በማምጣት ኢትዮጵያ የባህር በር ሊኖራት ይችላል፤ ይህ በአለም ላይ በኢትዮጵያ የአፋር ምድር ረባዳነት የተነሳ ተፈጥሮ የሰጠው እድል ነው! በኢትዮጵያ እና በኤርትራ መካከል አርተፊሻል ቦይ በመስራት ኢትዮጵያ የወደብ ባለቤት መሆን ትችላለች፡፡ እንደዚህ አይነት አጋጣሚ ሊፈጠር የቻለው፤ የኢትዮጵያ የአፋር ቦታ ከባህር ወለል በታች እስከ 110 … Read moreContinue Reading
- ብሄራዊ ባንክ የገንዘብ ቁጥጥሩን አጠንክሮ እንደሚገፋበት አስታወቀ፤ ህገወጥ የወርቅ አዘዋዋሪዎች ላይ እርምጃ እየተወሰደ ነው– የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ አዲስ የማቋቋሚያ ረቂቅ አዋጅ አዘጋጀ በአገሪቱ የሚታየውን የዋጋ አለመረጋጋት ለመግራት የግንዘብ ስርጭት ላይ ጥብቅ ቁጥጥር በማድረግ የተጀመረው ስራ ውጤት እያሳየ መሆኑ ተመለከተ፤ ተጠናክሮ ክምሩ እንደሚሰራበትና ግሽበትን በዓመቱ መጨረሻ 20 ከመቶ ለማድረስ መታቀዱ ተሰማ። ህገወጥ የወርቅ ነጋዴዎች ላይ ጥብቅ ቁጥጥርና የማበረታቻ መደረጉ ለውጥ ቢያሳይም በቂ እንዳልሆነ ተመለከተ። … Read moreContinue Reading
- የኮሚሽኑ የቀድሞ ሠራተኞች ከ40 ሚሊየን ብር በላይ የሙስና ክስ ጋር ተያይዞ ያቀረቡት የክስ መቃወሚያ ውድቅ ሆነየአዲስ አበባ እሳት እና አደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን የቀድሞ ሠራተኞች ከ40 ሚሊየን ብር በላይ የአልባሳት ግዢ ጋር ተያይዞ በቀረበባቸው የሙስና ወንጀል ክስ ያቀረቡት የክስ መቃወሚያ ውድቅ ተደረገ። ተከሳሾቹ ያቀረቡትን የክስ መቃወሚያ ውድቅ ያደረገው የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 3ኛ የሙስና ጉዳዮች ወንጀል ችሎት ነው። የፍትሕ ሚኒስቴር የሙስና ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ዐቃቤ … Read moreContinue Reading
- መንግስት የነዳጅ ድጎማን በህገወጥ መንገድ ሲጠቀሙ ነበሩ ያላቸውን 40 ሺህ ተሽከርካሪዎች ከስርአቱ አስወጣ፣ የሰርቁትን ይከፍላሉየታለመለት የነዳጅ ድጎማን ላልተገባ ዓላማ ሲጠቀሙ የነበሩ 40 ሺህ ተሽከርካሪዎች ከድጎማ ስርዓቱ እንዲወጡና ዕዳ እንዲከፍሉ መደረጉን የፕላንና ልማት ሚኒስትር ዶክተር ፍጹም አሰፋ ገለጹ። ሚኒስትሯ ይህን ያሉት የመንግሥት የ2016 የመጀመሪያ የሩብ ዓመት አፈጻጸም በተገመገመበት ወቅት ነው። የግምገማው ተሳታፊዎች መንግሥት የነዳጅ ድጎማን ጨምሮ በርካታ የህዝብ ተጠቃሚነትን የሚያረጋገጡ ተግባራትን ማከናወኑን አድንቀው፤ ሆኖም” ድጎማው … Read moreContinue Reading
- በዓመት አምስት ሚሊዮን ቶን ሲሚንቶ የሚያመርተው ፋብሪካ ከመጋቢት በሁዋላ የሲሚንቶ ዋጋ ወደ ነበረበት የሚመልሰ ነውበቀን 10 ሺህ ቶን ሲሚንቶ እንዲያመርት እቅድ ተይዞለት በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን እንሳሮ ወረዳ ለሚ ከተማ እየተገነባ ያለውን የለሚ ናሽናል ሲሚንቶ ፋብሪካ የግንባታ በመጋቢት ወር ይጠናቀቃል። ምርቱ በተባለው ወር ሲጀምር የሲሚንቶ ዋጋ አሁን ካለበት በግማሽ እንደሚወርድ ይጠበቃል። ከመጋቢት በሁዋላ ፋብሪካው በ50 በመቶ የሲሚንቶ እጥረቱን ያስወግዳል። ኢስት አፍሪካን ሆልዲንግ ኩባንያ … Read moreContinue Reading