የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ሌ/ጀነራል ታደሰ ወረደ በራያ አላማጣ ዳግም ወረራ እየተካሄደ መሆኑ ይፋ መደረጉን ተከትሎ በወቅታዊ ጉዳዮች ለክልሉ መገናኛ መግለጫ ሲሰጡ ” በህገ-መንግስት መሰረት የትግራይ ግዛታዊ አንድነት እንዲረጋገጥ ተፈናቃዮች ወደ ቄያቸው እንዲመለሱ ተስማምተዋል ” ብለዋል። በግልጽ የትግራይ ሃይሎች ስለያዟቸው አካባቢዎች ግን ያሉት ነገር የለም።
” በፕሪቶሪያ ውል ያልተፈፀሙት እንዲተገበሩ እየሰራን እንቀጥላለን ” ያሉት እኚሁ ባለስልጣን፣ ” የፕሪቶሪያ ውል የፈረምነው የተለያዩ የትግራይ ቦታዎች ከክልሉ አስተዳደር ውጭ በነበሩበት በርካታ ወገኖች ከቄያቸው በተፈናቅሉበት ጊዜ ነበር ” ብለዋል። አክለውም ” የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ውልን በጥንቃቄ መተግበር ይገባል ” ሲሉ ገልጸዋል።
” አሁን በመታየት ያለው ውጤት የጦርነቱ ውጤት እንጂ የጦርነቱ መነሻ አይደለም ” እንዳልሆነ ገልጸው ተነሳ የተባለው አዲስ ጦርነት የወቅታዊው ሁኔታ ውጤት እንደሆነ አድርገው ገልጸዋል።
” የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ትግራይ በሃይል የተያዘባት መሬት ሙሉ በሙሉ መልሳ የተሟላ ቁመናዋ መያዝ ፤ ተፈናቃዮች ወደ ቀያቸው መመለስ እንዲተገበሩ ያስገድዳል ይህ እንዲሆን ደግሞ በሃይል በተያዙ ቦታዎች ያሉ ታጣቂዎች መውጣትና ህጋዊ ያልሆነው አስተዳደር መፍረስ አለባቸው ” ብለዋል።
” ህጋዊ ያልሆኑ አስተዳደሮች ማፍረስና ታጣቂዎች ትጥቃቻውን ማስፈታት የፕሪቶሪያ ውል የመጀመሪያ ምዕራፍ ሲሆን ቀጥሎ የሚደረገው ሁሉ ሰላም ከተረጋገጠ በኋላ የሚሆን ነው ” ሲሉ ተናግረዋል።
” ተፈናቃዮች ሲመለሱ ክብራቸው ተጠብቆ ፣ የሚያስፈልጋቸው መሰረተ ልማት ሁሉ ተሟልቶ ሰብአዊ ድጋፍ ጨምሮ የተለያዩ ድጋፎች በማድረግ መሆን አለበት ” ያሉት ጀነራሉ ” አስተዳደርን በሚመለከት ቀበሌዎችና ወረዳዎችን የሚያስተዳድሩ ጊዚያዊ አስተዳደሮች ራሱ ህዝቡ ይመርጣል ” ብለዋል።
ዘላቂ መፍትሄን አስመልክቶ ” የፌደራል መንግስት አከባቢዎቹ በፌዴራል ስር ቆይተው ሪፈረንደም ይካሄድ የሚል አቋም ያለው ሲሆን በእኛ በኩል ደግሞ በአከባቢው ጊዚያዊ አስተዳደር ተቋቁሞ ወደ ትግራይ ይመለሱ የሚል አቋም ነው ያለው፤ ይህ የአቋም ልዩነት እስካሁን አልተፈታም እንዲፈታ ደግሞ ቀጣይ ሰላማዊ ትግል እናደርጋለን ” ብለዋል።
የጀነራሉን በመግለጫ ጠቅሶ ቲክቫህ ቃል በቃል የራያ አላማጣ አካባቢዎችን አስመልክቶ ዳግም በትግራይ ሃይሎች ስለመያዛቸው ባይገልጽም፣ ንግግራቸው ልክ የስምምነቱ አካል እንደሆነ አድርገው መግለጻቸው ከመንግስት ምላሽ የሚያስፈገው ጉዳይ ሆኗል።