የኢትዮጵያን መከላከያ ሰራዊት በአነስተኛና በድንገተኛ ግጭት በመበታተን መቆም የሚገባው ላይ ሆኖ አገሩን እንዳይከላከል ለማድረግ የተከፈተውን ዘመቻ ተረድቶ መዘጋጀት የወቅቱ ጥያቄ መሆኑንን ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አስታወቁ። በደረሰው ክፉ ድርጊት ስሜታቸውንም ገልጸዋል።
ምርጫን አስመልክቶ ዛሬ ከክልል መሪዎችና ሃፊዎች ጋር ውይይት ሲያደርጉና የስራ መመሪያ ሲሰጡ እንዳሉት በየአቅጣጫው ሽፍቶች ጥቃት የሚሰነዝሩት ሃይል ለማዳከም ነው። ኢትዮጵያን የሚወዱ ሁሉ በአንድ ላይ ህብረት አለመፍተራቸው ጉዳት እንዳለው ጠቅሰው ወቃሳም ሰንዝረዋል።
መከላከያን ፖሊስ ለማተናከር ሃይል ሲጠየቅ መልስ እንደሌለ፣ ሁሉም ቤቱ ተቀምጦ ሰላም ጠያቂ መሆኑ እርስ በርስ የሚጋጭ ተግባር እንደሆነ አመልክተው፣ ይህ ትክክል እንዳልሆነ ጠቁመዋል። አያይዘውም ” ሃሳብ ሲደርቅ ስድብ ይከተላል” በማለት የክልል አመራሮች ይህን ስድብ ወደ ጎን በመተው ምርጫ ላይ ትኩረት ሰጥተው እንዲሰሩ አበረታተዋል።
ምንም ይሁን ምን ከምርጫ ውጪ ሌላው መንገድ የመንግስትን እርምጃ አቋም ያስቀይር እንደሆን እንጂ ሌላ አማራጭ ስለማያስገኝ ሁከትን አቋራጭ ማድረግ እንደማይጠቅም ገልጸዋል። እሳቸውም ሆኑ ፓርቲያቸው ቃለ በገቡት መሰረት ፍትሃዊ ምርጫ የማድረግ ፍላጎታቸው እንደማይታጠፍ በመግለጽ ጥብቅ ማስተንቀቂያ አክለዋል።
መስከን፣ ሃላፊነት በተሞላው መንገድ ማሰብ፣ ከስሜት መውጣት እንደሚያስፈልግ በማውሳት፣ ጠላት ባስቀመጠው ቦይ መፍሰስ ከፍተኛ ዋጋ እንደሚያስከፍል ጠቁመዋል።
ማንም እንዳየው የጨረቃ ምርጫ አካሂደው አገር ለማተራመስ የሞከሩ ምን እንደደረሰባቸው በመግለጸ፣ አገር ለማተራመስና ለማፍረስ የቤት ስራ የውሰዱ በተመሳሳይ እንደሚፈርሱ ተናግረዋል።
ኢትዮጵያን የተሸከመ መሪና ድርጅት በረባውም ባልረባውም የአደባባይ ስድብ ሊያኮርፍ እንደመይገባ ለክልል አመራሮች አጽንዖት ሰጥተው የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ፣ ሃሳብ አዘጋጅተው መሸጥ ያልቻሉ ስድብን ማምረታቸው እንደማይገርም አመልክተዋል። አያይዘውም በዚህ መልኩ እንደማይቀጥልና ህጋዊ አካሄድ መከተልም አግባብ ሊሆን እንደሚችል ፍንጭ ሰጥተዋል።
” መስዋዕት እየተከፈለ እውቅና የሚነፈግ ከሆነ ድካም ያመጣል” ሲሉ አንዳንዶች መከላከያን ሊወርፉ መሞከራቸውን በመቃወም የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ድርጊቱ ነውር መሆኑንንም አስታውቀዋል። ሙሉውን ከቪዲዮው ያድመጡ
- አፍሪቃ ህብረት ምን አሰጋውና “ገንዘቤን ወደ ሌላ አገር ለማዛወር እያሰብኩ ነው” ሲል ተንሿከከ፤ የጾምና የፍስክ ዜናዎችባንኩ የክፍያ ሰነድ ቀረበለት። ማጣሪያ ጥያቄ ለህብረቱ አቀረበ። ሃሰት ሆኖ… Read more: አፍሪቃ ህብረት ምን አሰጋውና “ገንዘቤን ወደ ሌላ አገር ለማዛወር እያሰብኩ ነው” ሲል ተንሿከከ፤ የጾምና የፍስክ ዜናዎች
- የኢትዮጵያ ኤልክትሪክ ኃይል 300 ቢሊዮን ብር የንግድ ባንክ ዕዳ አለብኝ አለ፤ ዕዳውና የክፍያው ጫና እንደከበደውም አስታውቋልየኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከንግድ ባንክ 300 ቢሊዮን ብር ዕዳ እንዳለበት… Read more: የኢትዮጵያ ኤልክትሪክ ኃይል 300 ቢሊዮን ብር የንግድ ባንክ ዕዳ አለብኝ አለ፤ ዕዳውና የክፍያው ጫና እንደከበደውም አስታውቋል
- ዋና ዋና የሽግግር ፍትህ ፖሊሲ ይዘቶች – ሲጨመቁመግቢያ ሽግግር ፍትህ ጉልህ የመብት ጥሰቶች በተፈፀመባቸው ሀገራት ተጠያቂነትን ለማስፈን… Read more: ዋና ዋና የሽግግር ፍትህ ፖሊሲ ይዘቶች – ሲጨመቁ
- “የአማራ ክልል ሚሊሻዎች ትጥቅ ይፍቱ በሚል የሚሰራጩ መረጃዎች ‘ባልበላውም ጭሬ ላፍሰው’ ከሚል ቅዠት የተወለደ ቅጥፈት ነው”“የሚሊሻ ኀይሉን በተመለከተ የሚዘዋወረው መረጃ ፍጹም መሠረተ ቢስ ነው” ሲሉ… Read more: “የአማራ ክልል ሚሊሻዎች ትጥቅ ይፍቱ በሚል የሚሰራጩ መረጃዎች ‘ባልበላውም ጭሬ ላፍሰው’ ከሚል ቅዠት የተወለደ ቅጥፈት ነው”
- “የህዝባችንን ድምጽ የሚቀማና የሚያፍን የ’አማራ ስብስብ’ ለአማራ ክልል ተግዳሮት ሆኗል… ትህነግ ዘርፎ እያጋጋዘ ነው” አብን“የትግራይ ተወላጆች ትህነግ ለፈጸመው ወረራ፣ ዘረፋ፣ ማፈናቀልና የግድያ ተግባራት የተቀናጀ… Read more: “የህዝባችንን ድምጽ የሚቀማና የሚያፍን የ’አማራ ስብስብ’ ለአማራ ክልል ተግዳሮት ሆኗል… ትህነግ ዘርፎ እያጋጋዘ ነው” አብን