ሱዳን ተጨማሪ ሰራዊት ወደ ኢትዮጵያ ድንበር አስተጋለሁ አለች፤ ሊንዳ ቶማስ የሱዳን መንግስት የተረጋጋ እንዲሆን ሊታገዝ ይገባል ብለዋል

ካርቱም ላይ ከግብጽ ጋር የነበረው ምክክር ካለቀ በሁዋላ የሱዳን የፀጥታና የመከላከያ ምክር ቤት በቅርቡ በድንበር አካባቢ የኢትዮጵያን ወታደራዊ የመከላከያ ሃይሏን አተናክራለች በሚል በምስራቅ ሱዳን ድንበር ያሰማራውን ሃይል ለማጠናከር መወሰኑ ተሰማ። ተጨማሪ ሃይልም ወደ ስፍራው እንደሚልክ ይፋ ሆኗል።

የሱዳን ወታደራዊ ባለሥልጣናት ማክሰኞ ዕለት ከጋዳሬፍ ግዛት ጋር በሚዋሰነው በአማራ ክልል ተጨማሪ የኢትዮጵያ ጦር ተጨማሪ ወታደሮችን ማሰማሩን ለሱዳን ትሪቢዩን አስታወቁ ፡፡

የሱዳንን ወታደራዊ ባለስልጣናት ጠቅሶ ሱዳን ትሪቡን እንደዘገበው ውሳኔው የተወሰነው ባለፈው ሐሙስ በሉዓላዊው ምክር ቤት ኃላፊ አብደል ፋታህ አል-ቡርሃን በተመራው የፀጥታና የመከላከያ ም / ቤት መደበኛ ስብሰባ ላይ ውይይት ከተደረገበት በሁዋላ ነው።

እንደምንክንያት የቀረበው የኢትዮጵያ ሚሊሺያዎች በሱዳን አርሶ አደሮች ላይ ጥቃታቸውን አጠናክረው መቀጠላቸውና የተወሰኑትን ካገቱ በኋላ መሬታቸውን ጥለው እንዲወጡ አስገድደዋል በሚል የአንድ ወገን መረጃ በመጥቀስ ነው ሱዳን ትሪቡን ያስታወቀው።

ሱዳን የአማራ ሚሊሻ የሚለውን ጉዳይ ደጋግማ ብታነሳም ዋናው ጉዳይ ግን ግብጽ ለሰጠቻት የቤት ስራ መነሻ ምክንያት ለመፍጠር እንደሆነ ይታወቃል። በሱዳን ያለው አለመረጋጋት መርገብ እንዳለበት ከወትሮው በተለየ ሊሰራ እንደሚገባ በተመድ የዩናይትድ ስቴትስ አምባሳደር ሊንዳ ቶማስ ትግራይን አስመልክቶ ከአውሮፓ ህብረት ኮሚሽን ተወካዮችና ሌሎች ዓለም ዓቀፍ አካላት ጋር በተካሄደ የጠርጴዛ ዙሪያ ውይይት አንስተዋል።

ሱዳን የያዘችውን አቋም የማይደግፉ ባለስልጣናትና የወታደራዊ መኮንኖች መኖራቸው በሚሰማበት፣ የውስጥ አለመግባባቱና ትርምሱ በገነነበት፣ አመጽ በየቀኑ በሚስተናገድባት፣ የዳርፉር ጉዳይ እያገረሸ በሄደበትና የሱዳን ወደብ ከተማ አካባቢ በአስቸኳይ አዋጅ ስር ባለበት በአሁኑ ወቅት ቶማስ ሊንዳ ሱዳን ልትታገዝ እንደሚገባ አጽንዖት መስጠታቸው አካሄዱን ግልጽ እንደሚያደርገው ባለሙያዎች ወዲያው ነው የተቹት።

በሲኤኔን ጋዜጠኛ መሪነት በተካሄደው ኢትዮጵያን የመደብደብ ስብሰባ ሊንዳ ልክ እንደ ሱዳን ሁሉ የአማራን ስም በመጠቀስ ሲናገሩ ፊታቸው ላይ ከሚታየው ንዴት በላይ ድምጻቸውና ጥሪያቸው አንዳች ልዩ ጫና የመፍጠር ስሜት እንዳላቸው በሚያሳብቅ መልኩ ነበር።

ሊንዳ ብቻ ሳይሆኑ ሳማታን ፓወርም በተመሳሳይ ሱዳን ስለሟን እንድታስጠብቅ ልትረዳ ይገባል በሚል አንስተዋል። ሱዳን ወታደሮቿን ወደ ኢትዮጵያ ድንበር ለማንቀሳቀስ መወሰኗን በይፋ ማስታወቋን ተከትሎ ከኢትዮጵያ በኩል እስካሁን የተባለ ነገር የለም። ይሁን እንጂ በድንበር አካባቢ ኢትዮጵያ በቂ ዝግጅት እንዳላትና የህዳሴው ግድብ ዙሪያ ምን ቀልድ እንደሌለ ማስታወቋ፣ አካባቢው ላይ ለሚሞከር ማናቸውም ጥቃት ሙሉ ዝግጅት መኖሩን መግለጿና ሙከራ ለሚያደርጉ ማስጠንቀቂያ መስጠቷ አይዘነጋም። ሱዳን ሰልጥኖ ወደ ቢኒሻንጉል ሊዘልቅ የነበረ ሃይልም በቅርቡ ሙሉ በሙሉ መደምሰሱ ያታወሳል።

See also  በጎንደር ከተማ የተከሰተውን ግጭት አስመልክቶ ከአማራ ክልል መንግሥት የተሰጠ መግለጫ

  • “ደብረ ኤሊያስ ገዳም የደረሰበት ጉዳት የለም” ወረዳው፤ መከላከያ ስራውን መጨረሱ ተሰማ
    አካባባዊ በተለይም ገዳሙ ወታደራዊ ማስለጠኛ፣ የሚፈለጉ ሰዎች መመሸጊያ፣ ሃይማኖታዊ ዓላማውን የሳተ በመሆኑ በአባቶች፣ በሃይማኖት መሪዎች፣ በመንግስት ሃላፊዎችና ታውቃ ሰዎች ቢለመኑም ፈቃደኛ እንዳልሆኑ፣ በስተመጨረሻም ደብሩም ሆነ መኖኮሳቶች ምንም ሳይሆኑ መከላከያ ገብቶ ስራውን አከናውኖ መጨረሱ ተሰማ። በርካታ ታጣቂዎች ለመከላከያ እጃቸውን መስጠታቸውም ተገልጿል። ወረዳው መከላከያ ስራውን ጉዳት ሳያደርስ ማከናወኑን ይፋ ሲያደርግ እጅቻውን ስለሰጡናContinue Reading
  • አሮጌውን ወይን በአዲስ አቁማዳ ! የኖርንበት ፣ የቸከ የሰለቸ የፖለቲካ …
    የኢትዮጵያ ታሪክ የእርስ በእርስ ጦርነት civil war & strife ነው። ይሄንን ያደፈ ጉድለታችንን ማስተካከል የምንችለው መሀከለኛውን መንገድ የያዙ ስብስቦችን በማብዛት ነው። ችግሩ በእኛ ሀገር ፖለቲካ መሀከሉን መንገድ ልትይዝ ስትሞክር የሚወረወርብህ ፍላጻ መብዛቱ ነው። ለዚህ ጥሩ ምሳሌ ኢዜማ ነው። ህወሃትም ፣ የኦሮሞ ብሄረተኜችም ፣ በቅርብ የተፈለፈሉት የአማራ ብሄረተኞችም ለፓርቲው ያላቸውን ጥላቻContinue Reading
  • US Special Envoy for HoA Amb Mike Hammer to Visit Ethiopia
     US Special Envoy for the Horn of Africa Ambassador Mike Hammer will visit Ethiopia on May 31 – June 6. In Ethiopia, Ambassador Hammer will meet African Union officials on implementation of the November 2, 2022 Cessation of Hostilities Agreement (COHA). He will discuss progress and priorities including transitional justiceContinue Reading
  • በሽብር ወንጀል በተጠረጠሩ በ38 ግለሰቦች ላይ ተጨማሪ የ14 ቀን ጊዜ ተፈቀደ
    የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 1ኛ ጊዜ ቀጠሮ ችሎት በ3 መዝገብ የቀረቡ የ38 ተጠርጣሪዎችን ጉዳይ ተመልክቷል። ተጠርጣሪዎቹን ፍርድ ቤት ያቀረበው የፌደራል ፖሊስ መርማሪ በቀዳሚነት በነመላክ ምሳሌ መንግስቱ መዝገብ የተካተቱ 16 ግለሰቦችን እና በነደበበ በሻህ ውረድ መዝገብ የተካተቱ በ12 ተጠርጣሪዎች አጠቃላይ 26 ግለሰቦች ላይ የሽብር ወንጀል የጥርጣሬ መነሻውን በፅሁፍም በቃልምContinue Reading
  • ሟችን በጭፈራ የሚሸኘው ማህበረሰን
    በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በኮንሶ ዞን ውስጥ ተወልደው ያደጉት ዶ/ር ኦንጋዬ ኦዳታ በቅርቡ ነው አያታቸውን በሞት ያጡት። የሚወዷቸው አያታቸው ቀብር የተፈፀመው ግን ወዳጅ ዘመድ ተሰብስቦ ዘፍኖ እና ጨፍሮ በተከናወነ ሥነ ሥርዓነት መሆኑን ከቢቢሲ ጋር በነበራቸው ቆይታ ተናግረዋል። ሞት በሁሉም ዘንድ ሁሌም አዲስ ነው። በመጣ ቁጥር የሚያስደነግጥ በብዙ ማኅበረሰቦች ዘንድም ማቅ የሚያስለብስContinue Reading

Leave a Reply