ጦርነት በሌለበትና ተዋጊ የሆኑ ሁለት ኃይሎች በማይታዩበት ሁኔታ ተኩስ አቁሙ የሚለው የአሜሪካን ጥሪ ግራ የሚያጋባ መሆኑን የኢትዮጵያ ሶሻል ዴሞክራቲክ ፓርቲ (ኢሶዴፓ) ፕሬዚዳንትና የፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ ተናገሩ::
ፕሮፌሰር በየነ በተለይም ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንዳሉት በሰላም ተነጋግራችሁ ችግራችሁን ፍቱ የሚለው አባባል የተለመደ ነው፤ ነገር ግን ጦርነት በሌለበትና ተዋጊ የሆኑ ሁለት ኃይሎች በማይታዩበት ሁኔታ ተኩስ አቁሙ ማለት ግራ የሚያጋባ ነው::
እንደ ፕሮፌሰር በየነ ገለጻ ይህ አሁን ያሉትም የተኩስ አቁሙም ሆነ ተደራደሩ የሚለው ሃሳባቸው እውነታውን የሚያሳይ ነው ወይ ? ወይም ደግሞ ኢትዮጵያን የሚመለከት ነው፤ አይደለም? የሚለውን በጥንቃቄ ማየት ያስፈልጋል::
ይህ አባባል “ህወሓት አሁንም እየተዋጋ ነው፤ የኢትዮጵያ መንግሥትም በትግራይ ክልል ውስጥ ጦርነት ላይ ነው፤” የሚል እንደምታ ያለው ነው ፤ ያሉት ፕሮፌሰር በየነ ነገር ግን የመንግሥት አቋምም ሆነ መሬት ላይ ያለው እውነት ህገወጥ የሆኑ ኃይሎች ላይ እርምጃ በመውሰድ ወንጀል የፈጸሙትን አድኖ የመያዝ ሂደት መሆኑን አብራርተዋል::
በመሆኑም ጦርነት በሌለበትና ተዋጊ የሆኑ ሁለት ኃይሎች በማይታዩበት ሁኔታ ተኩስ አቁሙ ማለት ትንሽ ግራ የሚያጋባ በመሆኑ ይህንን አቋማቸውን ከቻሉ ሰላማዊ መንገድ ፈልጉ፤ የሚሸሹትንም ጁንታዎች ሽሽታችሁን አቁማችሁ ለህግ ተገዙ በማለት ለማስማማት ቢሞክሩ የተሻለ እንደሚሆንም ጠቅሰዋል::
በአገር ውስጥም ይሁን በዓለም አቀፍ ደረጃ ወንጀል ፈጽሞ የተደበቀን አካል አሳዶና አድኖ መያዝ ያለና ወደፊትም የሚሠራበት አካሄድ ነው ያሉት ፕሮፌሰር በየነ መንግሥት ይህንን እያደረገ ባለበት ሁኔታ ላይ እንዲሁም የታቀደ ወይም የተለዩ ሁለት ኃይሎች ኖረው ያልተከፈተን ጦርነት ተኩስ አቁሙ ማለት ግራ የገባው ውሳኔ ይመስላል ብለዋል::
ባለኝ መረጃ በሁለት ወገን የተደራጁ ወታደሮች ውጊያ እያደረጉ አይደለም ያሉት ፕሮፌሰር በየነ፤ መንግሥትም ሁኔታው ይህ ነው አላለም ፤ነገር ግን ወንጀለኞቹ ዛሬ ከተደበቁበት ዋሻ ነገ ደግሞ ወደሌላ እየሄዱ እንዳሉና እነሱን እያደነ መሆኑን ገልጿል፤ ይዞም ፍርድ ቤት ያቀረባቸው አሉ ብለዋል፡፡
እነርሱ እዚህ ውሳኔ ላይ የደረሱት ከሚሰጣቸው የተሳሳተ መረጃ በመነጨ ነው ያሉት ፕሮፌሰር በየነ መገናኛ ብዙሃኑ እንዳንገባ ተደረግን በማለት ይጮሁና ሲገቡ ደግሞ ሪፖርት የሚያደርጉት ያልሆነና የተሳሳተ፤ መሬት ላይ ያለውን እውነት የማያሳይ ነው፤ በሌላ በኩልም ዕርዳታ እንሰጣለን በማለት የሚመጡትም ሥራቸው የተዛባ መረጃን ማቅረብ ነው፤ እነሱ ደግሞ ይህንን ይዘው የተሳሳተ ውሳኔ በማሳለፍ ላይ ናቸው ብለዋል::
“አሁን እነሱ እንደሚሉት ግጭት ቢኖር ኖሮ እኮ በክልሉ ጊዜያዊ መንግሥትም ለማቋቋም አይቻልም ነበር፤ ነገር ግን ሁሉም እንደሚባለው ስላልሆነ በክልል እስከ ወረዳ ድረስ አስተዳዳሪዎች እየተሾሙ ነው፤ በመሆኑም የሚደርሳቸውን መረጃ ማጥራትና ነባራዊ ሁኔታውን መመልከት አለባቸው” ብለዋል ፕሮፌሰር በየነ::
መንግሥት እነሱ የሚሉትን ወይም የሚያደርጉትን ወደጎን በመተው ለህዝቡ የሚጠቅመውን፤ እነሱንም ተዓማኒ የሚያደርገውንና ህዝቡን ከህወሓት አስተሳሰብ አውጥቶ በትክክልኛ መስመር ላይ እንዲገኝ የሚያስችለውን አቅምና እውቀት መጨመር ላይ ጠንክሮ መሥራት እንዳለበትም ፕሮፌሰር በየነ ጠቁመዋል::
በተጨማሪም ህወሓቶች ወጣቱ በሙሉ ከእኛ ጋር ነው እያሉ ልቡን የሚያሸፍቱበትን እንዲሁም እነሱ በእብሪት የሚወጠሩበትን አካሄድ እንዲተው ለማድረግም ከፍተኛ የሆነ ሥራ መሥራትና የተግባር ሰው መሆን እንደሚያስፈልግ ፕሮፌሰር በየነ ተናግረዋል፡፡
እፀገነት አክሊሉ አዲስ ዘመን
- አፍሪቃ ህብረት ምን አሰጋውና “ገንዘቤን ወደ ሌላ አገር ለማዛወር እያሰብኩ ነው” ሲል ተንሿከከ፤ የጾምና የፍስክ ዜናዎችባንኩ የክፍያ ሰነድ ቀረበለት። ማጣሪያ ጥያቄ ለህብረቱ አቀረበ። ሃሰት ሆኖ ተገኘና ፖሊስ ተጠርጣሪዎቹን ያዘ። ጉዳዩ ወደ ህግ አመራ።… Read more: አፍሪቃ ህብረት ምን አሰጋውና “ገንዘቤን ወደ ሌላ አገር ለማዛወር እያሰብኩ ነው” ሲል ተንሿከከ፤ የጾምና የፍስክ ዜናዎች
- የኢትዮጵያ ኤልክትሪክ ኃይል 300 ቢሊዮን ብር የንግድ ባንክ ዕዳ አለብኝ አለ፤ ዕዳውና የክፍያው ጫና እንደከበደውም አስታውቋልየኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከንግድ ባንክ 300 ቢሊዮን ብር ዕዳ እንዳለበት ተገለጸ። የዕዳ ጫናውን ለማቃለል የባንክ ወልዱም ጭምር ተፅእኖ… Read more: የኢትዮጵያ ኤልክትሪክ ኃይል 300 ቢሊዮን ብር የንግድ ባንክ ዕዳ አለብኝ አለ፤ ዕዳውና የክፍያው ጫና እንደከበደውም አስታውቋል
- ዋና ዋና የሽግግር ፍትህ ፖሊሲ ይዘቶች – ሲጨመቁመግቢያ ሽግግር ፍትህ ጉልህ የመብት ጥሰቶች በተፈፀመባቸው ሀገራት ተጠያቂነትን ለማስፈን እና ተበዳዮችን ለመካስ ጥቅም ላይ ሲውል ቆይቷል፡፡ በሀገራችንም… Read more: ዋና ዋና የሽግግር ፍትህ ፖሊሲ ይዘቶች – ሲጨመቁ
- “የአማራ ክልል ሚሊሻዎች ትጥቅ ይፍቱ በሚል የሚሰራጩ መረጃዎች ‘ባልበላውም ጭሬ ላፍሰው’ ከሚል ቅዠት የተወለደ ቅጥፈት ነው”“የሚሊሻ ኀይሉን በተመለከተ የሚዘዋወረው መረጃ ፍጹም መሠረተ ቢስ ነው” ሲሉ ኮሎኔል ግርማ ገሰሰ አስታወቁ። “ቅጥፈት ነው” ያሉትና በፕሬዚዳንቱ… Read more: “የአማራ ክልል ሚሊሻዎች ትጥቅ ይፍቱ በሚል የሚሰራጩ መረጃዎች ‘ባልበላውም ጭሬ ላፍሰው’ ከሚል ቅዠት የተወለደ ቅጥፈት ነው”
- “የህዝባችንን ድምጽ የሚቀማና የሚያፍን የ’አማራ ስብስብ’ ለአማራ ክልል ተግዳሮት ሆኗል… ትህነግ ዘርፎ እያጋጋዘ ነው” አብን“የትግራይ ተወላጆች ትህነግ ለፈጸመው ወረራ፣ ዘረፋ፣ ማፈናቀልና የግድያ ተግባራት የተቀናጀ የፖለቲካና የሚዲያ ድጋፍ ሰጥተዋል። በተለይም በትግራይ ክልል መቀሌ… Read more: “የህዝባችንን ድምጽ የሚቀማና የሚያፍን የ’አማራ ስብስብ’ ለአማራ ክልል ተግዳሮት ሆኗል… ትህነግ ዘርፎ እያጋጋዘ ነው” አብን