Ethiopia | የኪነ ሀውልት ስራው ሠዓሊና ቀራፂ በቀለ መኮንን ነው::
ከኪነህንፃው እስከ ኪነ ሐውልቱ ድረስ የከያኒያን የእውቀትና የጥበብ አሻራ ያረፈበት ቤተመጽሐፍት
(ይትባረክ ዋለልኝ)
ትላንት የተመረቀው ቤተ መጻሕፍት ‹አብርሆት Enlightenment› ይሰኛል። ቤተመፅሐፍቱ ከውጭ ጀምሮ ከኪነህንፃው እስከ ኪነ ሐውልቱ ድረስ የከያኒያን የእውቀትና የጥበብ አሻራ ያረፈበት ቤተመፅሐፍት ነው:: በተለይ በአውሮፓ አገሮች ውስጥ የሚገነቡ ህንፃዎችና ሁል ጊዜ እንደቀናሁ ነበር የኖርኩት:: አብርሆት ቤተመፅሐፍ ህንፃው ከውጫዊ ገፅታው ጨምሮ የቤተመፅሐፋን ሃሳብና ርዕይ መሰረት አድርጎ እንደተሰራ ያመለክታል:: በሌላው ሐገር የምንቀናው የሐገርን ቁሳዊና መንፈሳዊ እሴትን የያዘ የህንፃ ግንባታን በአብርሆት ቤተመፅሐፍ ላይ መመልከታችን ነገ ለኪነ ህንፃ ባለሙያዎች ብቻ ሳይሆን በመንግስትም ሆነ በግል ለሚሰሩ የህንፃ ግንባታዎች እንደ ማዕዘን ድንጋይ እንዲቆጠር ያደርገዋል ::
ጠቅላይ ሚኒስቴር አብይ አህመድ ትላንት በምርቃቱ ላይ ስለ ቤተመፅሐፍቱ ዓላማና ኪነህንፃውን አስመልክተው ሲናገሩ “ከሥነ ሕንጻው ጀምሮ ዕውቀትንና ታሪክን እንዲያንጸባርቅ ተደርጎ የተገነባ ነው። ‹አብርሆት ቤተመፅሐፍ ዋና ዓላማውም እውነትና ዕውቀት ነጻ የሚያወጣውን ማኅበረሰብ ለመመሥረት ስለሆነ ነው።
ኢትዮጵያ ለልጆቿ የሥልጣኔን መንገድ መርጣለች። ለጠላቶቿ ደግሞ ክንደ ብርቱ ሆና ትጠብቃቸዋለች። የሥልጣኔው መንገድ ደግሞ መማር፣ መመራመር፣ መወያየት፣ መከራከር፣ በሐሳብ መሸናነፍ፣ ዕውቀትን ማነፍነፍ፣ በአመክንዮ፣ በማስረጃና በመረጃ ላይ መመሥረት ናቸው። ” ነበር ያሉት ::
ሌለው አብርሆት ቤተመፅሐፍ ደጅ ላይ የቆመውን ኪነ ሐውልት ሰራው ነው:: ይህ የኪነ ሐውልት ስራ ለህንፃውና ለቤተመፅሐፍቱ ግዙፍ ጌጥና ውበት እንዲላበስ አድርጎታል:: ይህንየኪነ ሐውልት ስራ የሰራው ሰዓሊና ቀራፂ በቀለ መኮንን ነው:: በቀለ መኮንን ሐገራችን ካሏት የኪነሐውልት ስራ በለሙያዎች መካከል አንዱ ነው::
ስለዚህ የኪነ ሃውልት ትርጏሜና አጠቃላይ ስራውን በተመለከተ እንዲነግረኝ በስልክ ጠይቄው ነበር:: በቀለ መኮንንም አጠቃላይ ስለኪነ ሀውልቱ ያዘጋጀሁት ፁሑፍ ስላለ ለምን አልክልህም አልኝ :: እኔም የላከልኝ ፁሑፍ ይሄው ለእናንተ አድርሻለሁ::
“በአዲሱ የአብርሆት የህዝብ ቤተመፃሕፍት ደጃፍ የቆመው ኪነ ሀውልት በቅርፁ ፣ የስነውበትን ደስታ በሚፈጥር ቀረፃና የልጅነትን ደፋር ነፃነት ባጣመረ መልክ የተዋቀረ ነው። ከቅርብም ከሩቅም በሰዎች መተላለፊያ መንገድ ዳር በመሆኑ ለሁሉም አይኖች የተጋለጠ ነው።
ወደ መፃሕፍት ቤቱ ዘልቀው ኮስታራ ንባብ ከመጀመራቸው በፊት ሁሉም ተመልካቾች ባለፉበት የልጅነት ወራት ተናፋቂና አስገራሚ ድርጊት ዘና የሚሉበትን ዕድል እንዲፈጥር ሆን ተብሎ የተመረጠ ነው ይዘቱ ።
ከነሀስ ቀልጦ የተሰራው ህፃን በልጅነት ነፃነቱ ከዚህ ዓለም ማናቸውም ተፅዕኖ ነፃ ስለሆነ ነባር የዕውቀትና የመረጃ ክምር ላይ ተኝቶ ባደግንባቸው ፊደልና ቁጥር የተሰራ ሉል/ ዓለም ጋር ሞቅ ያለ ጨዋታ ይዟል። ይጠይቃል ይገረማል ይፈልጋል።እያደር ሲጎለምስ የሚፈራውን ገለባብጦና ተገለባብጦ ራሱንና አካባቢውን የማየት ድፍረት በዚች ዕድሜ ላይ ጀምራ እዛው ላይ የምታበቃ ድንቅ የቅፅበት ዘመን ናት።
ሁሉም ሰው ኋላ ተመሳሳይ ሰልፍ ውስጥ መግባቱ ባይቀርም ከርሞ በሚያጣው በነፃነቱ ዘመን የታደለውን ተሰጥዖ በዚህ ቅርፅ ውስጥ ማስቀረት ዋናው የዚህ ቅርፅ ዒላማ ነው ። የቅርፁ ትልቅ ተሸካሚ መሠረት ደግሞ እንደተፈጠረ የተተወ ትልቅ አለት ሲሆን ( subliminal )ውበትን ከሌላው የኤስቴቲክ ቀመር ጋር እንዲያዋህድና ግርምታን እንዲጨምር የተመረጠ ነው ።
ህፃኑና የፊደል ሉል ደግሞ በቀለም ፣በመጠን በቴክስቸር፣ በእይታ ክብደትና ቅለት ተናበው የተቀናበሩ የቅርፁ ይዘትና ቅርፅ ተጫዋችና አጫዋች ኤለመንቶች ናቸው።
በቀለ መኮንን 2021
በቄ እንኳን ደስ ያለህ!!
- ሶማሌላንድ የባህር በር ስምምነቱ በሁለት ወር ውስጥ ይቋጫል አለች፤ “መንግስት ውሉን ትቶታል” አቶ ኤሊያ መሰረትዜናው ከተሰማ ጀምሮ በከፍተኛ የተቃውሞ መግለጫና ማስተንቀቂያ የታጀበው የኢትዮጵያና የሶማሌላንድ ስምምነት ወደ መገባደዱ እያመራ እንደሆነ ተገለጸ። ለውጭ አገር ሚዲያዎች ዜና የሚያቀብሉና… Read more: ሶማሌላንድ የባህር በር ስምምነቱ በሁለት ወር ውስጥ ይቋጫል አለች፤ “መንግስት ውሉን ትቶታል” አቶ ኤሊያ መሰረት
- የነዳጅ ድጎማን በማጭበርበር የሙስና ወንጀል ለተጠረጠሩ በስር ፍ/ቤት የተሰጠ ዋስትና ፀናላቸው፤ ከአገር አይወጡምየፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የትራንስፖርት ስምሪትና የነዳጅ ድጎማን በማጭበርበር ሙስና ወንጀል ለተጠረጠሩ 11 ግለሰቦች በስር ፍ/ቤት የተሰጠውን ዋስትና አፀና። ፍርድ ቤቱ… Read more: የነዳጅ ድጎማን በማጭበርበር የሙስና ወንጀል ለተጠረጠሩ በስር ፍ/ቤት የተሰጠ ዋስትና ፀናላቸው፤ ከአገር አይወጡም
- መንግስት ስድተኞችን አልቀበልም በማለቱ የአውሮፓ ኅብረት በኢትዮጵያውያን ላይ ጊዜያዊ የቪዛ ገደብ ጣለየአውሮፓ ኅብረት በኢትዮጵያውያን ላይ ጊዜያዊ የቪዛ ገደብ ጣለ ምክንያቱም “የኢትዮጵያ መንግሥት በሕገ ወጥ መንገድ የአውሮፓ ኅብረት አገራት ውስጥ የሚኖሩ ዜጎቹን መልሶ… Read more: መንግስት ስድተኞችን አልቀበልም በማለቱ የአውሮፓ ኅብረት በኢትዮጵያውያን ላይ ጊዜያዊ የቪዛ ገደብ ጣለ
- “ሰራ ሰራ አድርጌ ቶሎ እመለሳለሁ” ሚሊየነሩ የሸኔ የ”ነጻነት” ታጋይ ወደ ጫካ ሲገባ ስንብት ላይ የተናገረውየሚነሳው ጉዳዩ ልብ ሰባሪ ነው፣ ያስቃል፣ ያዝናናል፣ ያስገርማል፣ ያሳዝናል፣ ይቀፋል፣ ያሳፍራል፣ ለማመን ያስቸግራል … አንባቢ ስም ይስጠው። እኔ ስጽፈው ግን በሃፍረት… Read more: “ሰራ ሰራ አድርጌ ቶሎ እመለሳለሁ” ሚሊየነሩ የሸኔ የ”ነጻነት” ታጋይ ወደ ጫካ ሲገባ ስንብት ላይ የተናገረው
- ሕገ ወጥ የጦር መሳሪያና የደኅንነት ስጋት – አቅራቢ፣ ፈላጊ፣ ነጋዴ፣ ደላላ ተገናኙና መደበኛ ገበያ ሆነ!በፖለቲካም ሆነ በአካባቢያዊ አጀንዳ ነፍጥ ያነገቡ እና ጦርነትን አማራጭ አድርገው የሚንቀሳቀሱ ኢ -መደበኛ አደረጃጀቶች ሁሉ የጦር መሳሪያ ፍላጎት ይኖራቸዋል፡፡ የጦር መሳሪያ… Read more: ሕገ ወጥ የጦር መሳሪያና የደኅንነት ስጋት – አቅራቢ፣ ፈላጊ፣ ነጋዴ፣ ደላላ ተገናኙና መደበኛ ገበያ ሆነ!