Ethiopia | የኪነ ሀውልት ስራው ሠዓሊና ቀራፂ በቀለ መኮንን ነው::
ከኪነህንፃው እስከ ኪነ ሐውልቱ ድረስ የከያኒያን የእውቀትና የጥበብ አሻራ ያረፈበት ቤተመጽሐፍት
(ይትባረክ ዋለልኝ)
ትላንት የተመረቀው ቤተ መጻሕፍት ‹አብርሆት Enlightenment› ይሰኛል። ቤተመፅሐፍቱ ከውጭ ጀምሮ ከኪነህንፃው እስከ ኪነ ሐውልቱ ድረስ የከያኒያን የእውቀትና የጥበብ አሻራ ያረፈበት ቤተመፅሐፍት ነው:: በተለይ በአውሮፓ አገሮች ውስጥ የሚገነቡ ህንፃዎችና ሁል ጊዜ እንደቀናሁ ነበር የኖርኩት:: አብርሆት ቤተመፅሐፍ ህንፃው ከውጫዊ ገፅታው ጨምሮ የቤተመፅሐፋን ሃሳብና ርዕይ መሰረት አድርጎ እንደተሰራ ያመለክታል:: በሌላው ሐገር የምንቀናው የሐገርን ቁሳዊና መንፈሳዊ እሴትን የያዘ የህንፃ ግንባታን በአብርሆት ቤተመፅሐፍ ላይ መመልከታችን ነገ ለኪነ ህንፃ ባለሙያዎች ብቻ ሳይሆን በመንግስትም ሆነ በግል ለሚሰሩ የህንፃ ግንባታዎች እንደ ማዕዘን ድንጋይ እንዲቆጠር ያደርገዋል ::

ጠቅላይ ሚኒስቴር አብይ አህመድ ትላንት በምርቃቱ ላይ ስለ ቤተመፅሐፍቱ ዓላማና ኪነህንፃውን አስመልክተው ሲናገሩ “ከሥነ ሕንጻው ጀምሮ ዕውቀትንና ታሪክን እንዲያንጸባርቅ ተደርጎ የተገነባ ነው። ‹አብርሆት ቤተመፅሐፍ ዋና ዓላማውም እውነትና ዕውቀት ነጻ የሚያወጣውን ማኅበረሰብ ለመመሥረት ስለሆነ ነው።
ኢትዮጵያ ለልጆቿ የሥልጣኔን መንገድ መርጣለች። ለጠላቶቿ ደግሞ ክንደ ብርቱ ሆና ትጠብቃቸዋለች። የሥልጣኔው መንገድ ደግሞ መማር፣ መመራመር፣ መወያየት፣ መከራከር፣ በሐሳብ መሸናነፍ፣ ዕውቀትን ማነፍነፍ፣ በአመክንዮ፣ በማስረጃና በመረጃ ላይ መመሥረት ናቸው። ” ነበር ያሉት ::
ሌለው አብርሆት ቤተመፅሐፍ ደጅ ላይ የቆመውን ኪነ ሐውልት ሰራው ነው:: ይህ የኪነ ሐውልት ስራ ለህንፃውና ለቤተመፅሐፍቱ ግዙፍ ጌጥና ውበት እንዲላበስ አድርጎታል:: ይህንየኪነ ሐውልት ስራ የሰራው ሰዓሊና ቀራፂ በቀለ መኮንን ነው:: በቀለ መኮንን ሐገራችን ካሏት የኪነሐውልት ስራ በለሙያዎች መካከል አንዱ ነው::

ስለዚህ የኪነ ሃውልት ትርጏሜና አጠቃላይ ስራውን በተመለከተ እንዲነግረኝ በስልክ ጠይቄው ነበር:: በቀለ መኮንንም አጠቃላይ ስለኪነ ሀውልቱ ያዘጋጀሁት ፁሑፍ ስላለ ለምን አልክልህም አልኝ :: እኔም የላከልኝ ፁሑፍ ይሄው ለእናንተ አድርሻለሁ::
“በአዲሱ የአብርሆት የህዝብ ቤተመፃሕፍት ደጃፍ የቆመው ኪነ ሀውልት በቅርፁ ፣ የስነውበትን ደስታ በሚፈጥር ቀረፃና የልጅነትን ደፋር ነፃነት ባጣመረ መልክ የተዋቀረ ነው። ከቅርብም ከሩቅም በሰዎች መተላለፊያ መንገድ ዳር በመሆኑ ለሁሉም አይኖች የተጋለጠ ነው።
ወደ መፃሕፍት ቤቱ ዘልቀው ኮስታራ ንባብ ከመጀመራቸው በፊት ሁሉም ተመልካቾች ባለፉበት የልጅነት ወራት ተናፋቂና አስገራሚ ድርጊት ዘና የሚሉበትን ዕድል እንዲፈጥር ሆን ተብሎ የተመረጠ ነው ይዘቱ ።
ከነሀስ ቀልጦ የተሰራው ህፃን በልጅነት ነፃነቱ ከዚህ ዓለም ማናቸውም ተፅዕኖ ነፃ ስለሆነ ነባር የዕውቀትና የመረጃ ክምር ላይ ተኝቶ ባደግንባቸው ፊደልና ቁጥር የተሰራ ሉል/ ዓለም ጋር ሞቅ ያለ ጨዋታ ይዟል። ይጠይቃል ይገረማል ይፈልጋል።እያደር ሲጎለምስ የሚፈራውን ገለባብጦና ተገለባብጦ ራሱንና አካባቢውን የማየት ድፍረት በዚች ዕድሜ ላይ ጀምራ እዛው ላይ የምታበቃ ድንቅ የቅፅበት ዘመን ናት።
ሁሉም ሰው ኋላ ተመሳሳይ ሰልፍ ውስጥ መግባቱ ባይቀርም ከርሞ በሚያጣው በነፃነቱ ዘመን የታደለውን ተሰጥዖ በዚህ ቅርፅ ውስጥ ማስቀረት ዋናው የዚህ ቅርፅ ዒላማ ነው ። የቅርፁ ትልቅ ተሸካሚ መሠረት ደግሞ እንደተፈጠረ የተተወ ትልቅ አለት ሲሆን ( subliminal )ውበትን ከሌላው የኤስቴቲክ ቀመር ጋር እንዲያዋህድና ግርምታን እንዲጨምር የተመረጠ ነው ።
ህፃኑና የፊደል ሉል ደግሞ በቀለም ፣በመጠን በቴክስቸር፣ በእይታ ክብደትና ቅለት ተናበው የተቀናበሩ የቅርፁ ይዘትና ቅርፅ ተጫዋችና አጫዋች ኤለመንቶች ናቸው።
በቀለ መኮንን 2021
በቄ እንኳን ደስ ያለህ!!
- ሸኔ መከፈሉ ተሰማ፤ በሺዎች የሚቆጠሩ ታጣቂዎቹ እጅ እየሰጡ ነው፤ ተማራኪዎቹ ድርጅቱ መፈረካከሱን አስታወቀ“የህግ የበላይነት ለማስከበር እየተወሰደ ያለዉን እርምጃ መቋቋም የተሳናቸው በሺዎች የሚቆጠሩ የአሸባሪዉ ሸኔ አባላት ለመንግስት እጅ ሰጡ” ሲል የዘገቡት መገናኛዎች እንዳሉት ድርጅቱ ቁመናው ፈርሷል። በቅርቡ በታንዛንያ ለስምምነት ብዙ ርቀት ከተኬደና ከንግገሩ መልካም ዜና የተጠበቀ ባለበት ወቅት ስምምነት ላይ እንዳልተደረሰ መንግስት ይፋ ማድረጉ ይታወሳል። በሰላም ንግግሩ የተኩስ ማቆም ስምምነት ተደርሶ እንደነበር፣ አነጋጋሪ … Read moreContinue Reading
- ሰው ሰራሽ ቦይ በመገንባት ቀይ ባህርን መቀላቀል የኢትዮጵያ ሌላ አማራጭ?አርተፊሻል ቦይ በመገንባት ቀይ ባህርን ወደ ኢትዮጵያ በማምጣት ኢትዮጵያ የባህር በር ሊኖራት ይችላል፤ ይህ በአለም ላይ በኢትዮጵያ የአፋር ምድር ረባዳነት የተነሳ ተፈጥሮ የሰጠው እድል ነው! በኢትዮጵያ እና በኤርትራ መካከል አርተፊሻል ቦይ በመስራት ኢትዮጵያ የወደብ ባለቤት መሆን ትችላለች፡፡ እንደዚህ አይነት አጋጣሚ ሊፈጠር የቻለው፤ የኢትዮጵያ የአፋር ቦታ ከባህር ወለል በታች እስከ 110 … Read moreContinue Reading
- ብሄራዊ ባንክ የገንዘብ ቁጥጥሩን አጠንክሮ እንደሚገፋበት አስታወቀ፤ ህገወጥ የወርቅ አዘዋዋሪዎች ላይ እርምጃ እየተወሰደ ነው– የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ አዲስ የማቋቋሚያ ረቂቅ አዋጅ አዘጋጀ በአገሪቱ የሚታየውን የዋጋ አለመረጋጋት ለመግራት የግንዘብ ስርጭት ላይ ጥብቅ ቁጥጥር በማድረግ የተጀመረው ስራ ውጤት እያሳየ መሆኑ ተመለከተ፤ ተጠናክሮ ክምሩ እንደሚሰራበትና ግሽበትን በዓመቱ መጨረሻ 20 ከመቶ ለማድረስ መታቀዱ ተሰማ። ህገወጥ የወርቅ ነጋዴዎች ላይ ጥብቅ ቁጥጥርና የማበረታቻ መደረጉ ለውጥ ቢያሳይም በቂ እንዳልሆነ ተመለከተ። … Read moreContinue Reading
- የኮሚሽኑ የቀድሞ ሠራተኞች ከ40 ሚሊየን ብር በላይ የሙስና ክስ ጋር ተያይዞ ያቀረቡት የክስ መቃወሚያ ውድቅ ሆነየአዲስ አበባ እሳት እና አደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን የቀድሞ ሠራተኞች ከ40 ሚሊየን ብር በላይ የአልባሳት ግዢ ጋር ተያይዞ በቀረበባቸው የሙስና ወንጀል ክስ ያቀረቡት የክስ መቃወሚያ ውድቅ ተደረገ። ተከሳሾቹ ያቀረቡትን የክስ መቃወሚያ ውድቅ ያደረገው የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 3ኛ የሙስና ጉዳዮች ወንጀል ችሎት ነው። የፍትሕ ሚኒስቴር የሙስና ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ዐቃቤ … Read moreContinue Reading
- መንግስት የነዳጅ ድጎማን በህገወጥ መንገድ ሲጠቀሙ ነበሩ ያላቸውን 40 ሺህ ተሽከርካሪዎች ከስርአቱ አስወጣ፣ የሰርቁትን ይከፍላሉየታለመለት የነዳጅ ድጎማን ላልተገባ ዓላማ ሲጠቀሙ የነበሩ 40 ሺህ ተሽከርካሪዎች ከድጎማ ስርዓቱ እንዲወጡና ዕዳ እንዲከፍሉ መደረጉን የፕላንና ልማት ሚኒስትር ዶክተር ፍጹም አሰፋ ገለጹ። ሚኒስትሯ ይህን ያሉት የመንግሥት የ2016 የመጀመሪያ የሩብ ዓመት አፈጻጸም በተገመገመበት ወቅት ነው። የግምገማው ተሳታፊዎች መንግሥት የነዳጅ ድጎማን ጨምሮ በርካታ የህዝብ ተጠቃሚነትን የሚያረጋገጡ ተግባራትን ማከናወኑን አድንቀው፤ ሆኖም” ድጎማው … Read moreContinue Reading