በክልሉ እየታየ ያለው የሰላም እጦት በኢንቨስትመንቱ ላይ ቀጥተኛ የኾነ ተጽእኖ እያሳደረ እንደኾነ ነው የአማራ ክልል ኢንዱስትሪ እና ኢንቨስትመንት ቢሮ የገለጸው፡፡
እየታየ ያለው አለመረጋጋት ወደ ክልሉ እየገባ ያለውን እና ለመግባት በሂደት ላይ የነበረውን ኢንቨስትመንት እንደሚያስቀር ተገልጿል። ይህ ደግሞ በክልሉ ምጣኔ ሃብት ላይ ጉዳት እንደሚያስከትል ነው ቢሮው ያስገነዘበው።
የአማራ ክልል ኢንዱስትሪ እና ኢንቨስትመንት ቢሮ የሕዝብ ግንኙነት ኀላፊ ይሄነው ዓለም እንዳሉት ሰላም የሌለው ክልል አልሚዎችን ሊስብ አይችልም፡፡ አልሚዎች ለዳግም ኢንቨስትመንት በተለይም አዳዲስ ማሽኖችን ለማስገባት ያላቸውን ፍላጎት እንደሚቀንስም አብራርተዋል፡፡
ሰላም ከሌለ ኢንቨስትመንቱ አትራፊ ስለማይኾን አዳዲስ የሥራ እድል መፍጠር እንደሚሳነው እና ምርትም ማምረት እንደማይቻል አስገንዝበዋል፡፡
አሁን ላይ ያለው አለመረጋጋት የጥሬ እቃ ዝውውርን እየገታ በመኾኑ ወደ ውጭ የሚላኩ ምርቶችን ማምረት እንዳልተቻለ የሚናገሩት የሕዝብ ግንኙነት ኀላፊው ጉዳዩ የውጭ ምንዛሬን ለማግኘት አስቸጋሪ ነው ብለዋል፡፡
አቶ ይሄነው በሰላም መደፍረሱ ምክንያት ተጨማሪ ምርት አምርቶ በገበያው ላይ የሚታየውን የዋጋ መናር ለመቀነስ አስቸጋሪ እንዳደረገውም ነው ያስገነዘቡት፡፡
እየተፈጠረ ባለው ችግር ዋነኞቹ ተጠቂዎች ፋብሪካዎች ኾነዋል ፤ ይህም በፋብሪካዎቹ የሚሠሩ ሠራተኞችን ከሥራ እያፈናቀለ ስለመኾኑ ነው ያብራሩት፡፡ ባለፈው ጊዜ በተከሰተው አለመረጋጋት ብቻ ከ3 ሺህ በላይ የፋብሪካ ሠራተኞች ከሥራ ገበታቸው ስለመፈናቀላቸው ነው የገለጹት፡፡
በተለይም እስከ 8 የሚጠጉ የእርሻ ኢንቨስትመንቶች ላይ ጉዳት በመድረሱም ክልሉ እየተጎዳ ስለመኾኑ ነው ያስገነዘቡት፡፡
ከዘጠኝ በላይ በሚኾኑ የአበባ ልማት ዘርፎች ላይ ጉዳት በመድረሱ በዓመት ከ9 ሚሊዮን ዶላር በላይ ገቢ መታጣቱንም አብራርተዋል፡፡
የክልሉን ኢኮኖሚውን ለማሳደግ በክልሉ ያለውን ችግር ለመቅረፍ እና አሁን የተጀመረውን አንጻራዊ ሰላም ለማስቀጠል የሁሉንም የክልሉን ሕዝብ ለሰላም መረባረብን ይጠይቃል። (አሚኮ)
- Ethiopia Working To Secure New Development Bank MembershipThe Ministry of Foreign Affairs disclosed that Ethiopia is working hard to become member of BRICS’ New Development Bank. In… Read more: Ethiopia Working To Secure New Development Bank Membership
- የትግራይ ክልል ታጣቂዎች ዳግም ዝርፊያ እያፈጸሙ ነው፤ የተማሪዎች መጽሃፍትን “የአማራ ክልል ናቸው እየሉ ቀደዋል”በአላማጣ ከተማ በተለየ መልኩ የትግራይ ክልል ታጣቂዎች በከተማዋ ውስጥ እንደሚንቀሳቀሱ ነዋሪዎች መመስከራቸውን ቢቢሲ አስታወቀ። ይህ የተገለጸው ከአለማጣ እና አካባቢው የተፈናቀሉ… Read more: የትግራይ ክልል ታጣቂዎች ዳግም ዝርፊያ እያፈጸሙ ነው፤ የተማሪዎች መጽሃፍትን “የአማራ ክልል ናቸው እየሉ ቀደዋል”
- በዘንድሮው ዓመት የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ኢትዮጵያ ሰባት ነጥብ ሁለት ቢሊዮን ችግኝ ልትተክል ነውለዘንድሮ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር 6 ነጥብ 5 ቢሊየን ችግኝ ለመትከል ዕቅድ መያዙንna ለዚህም ተግባራዊነት ከሰባት ነጥብ ሁለት ቢሊየን በላይ ችግኝ… Read more: በዘንድሮው ዓመት የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ኢትዮጵያ ሰባት ነጥብ ሁለት ቢሊዮን ችግኝ ልትተክል ነው
- አፍሪካ ህብረት ” የውጭ ምንዛሪ ሒሳቡን ወደ ሌላ ሀገር ሊያዘዋውር ነው” የሚለው ዜና ሃሰት መሆኑን አረጋግጠአፍሪካ ህብረት የውጭ ምንዛሬ አካውንቱን ወደ ሌላ አገር እንደሚያዘዋውር ተጠቅሶ በህብረቱ ስም የወጣው ዜና ሃሰት፣ ሆን ተብሎ የተቀነባበረ መሆኑን መንግስት… Read more: አፍሪካ ህብረት ” የውጭ ምንዛሪ ሒሳቡን ወደ ሌላ ሀገር ሊያዘዋውር ነው” የሚለው ዜና ሃሰት መሆኑን አረጋግጠ
- አፍሪቃ ህብረት ምን አሰጋውና “ገንዘቤን ወደ ሌላ አገር ለማዛወር እያሰብኩ ነው” ሲል ተንሿከከ፤ የጾምና የፍስክ ዜናዎችባንኩ የክፍያ ሰነድ ቀረበለት። ማጣሪያ ጥያቄ ለህብረቱ አቀረበ። ሃሰት ሆኖ ተገኘና ፖሊስ ተጠርጣሪዎቹን ያዘ። ጉዳዩ ወደ ህግ አመራ። አሁን ምኑ… Read more: አፍሪቃ ህብረት ምን አሰጋውና “ገንዘቤን ወደ ሌላ አገር ለማዛወር እያሰብኩ ነው” ሲል ተንሿከከ፤ የጾምና የፍስክ ዜናዎች