ተሃድሶ ኮሚሽን ትጥቅ ከፈቱ የሸኔ ታጣቂዎች ጋር ተወያየ

ብሔራዊ ተሃድሶ ኮሚሽን የሰላም ጥሪን ተቀብለው ትጥቅ ከፈቱ እና ወደ ሰላማዊ ሕይወት ለመመለስ ከወሰኑ የሸኔ የቀድሞ ታጣቂዎች ጋር መወያየቱን የኮሚሽኑ ኮሚሽነር አምባሳደር ተሾመ ቶጋ ገለጹ።

ታጣቂዎቹ መሣሪያ በማስቀመጥ ወደ ሰላማዊ ሕይወት ተመልሰው በሀገሪቱ ሰላም፣ ዴሞክራሲ ግንባታ እና ልማት ውስጥ ለመሳተፍ የወሰኑ መሆናቸውን አምባሳደር ተሾመ ቶጋ በማኅበራዊ ትሥሥር ገጻቸው ባሰፈሩት መልእክት አስታውቀዋል።

እነዚህ የቀድሞ ታጣቂዎች በኮሚሽኑ ብሔራዊ የተሃድሶ ፕሮግራም ውስጥ ለመሳተፍ እንደተስማሙም የገለጹት ኮሚሽነሩ፣ “ሌሎችም የእነዚህን ታጣቂዎች ፈለግ እንደሚከተሉ ተስፋ አደርጋለሁ” ብለዋል። OBN

See also  ውድመትና ዘረፋ የደረሰበት የአቡነ ዮሴፍ ተራራ የሕዋ ምርምር ጣቢያን መልሶ ለመገንባት እየተሰራ ነው

Leave a Reply