በአማራ ክልል የተፈጠረውን ጦርነትና የክልሉን አሁናዊ ሁኔታ በመጠቀም ትህነግ “ተወሰደብኝ” የሚላቸውን አካባቢዎች ለማስመለስ ውጊያ እንደሚከፍት ሲገለጽ ሰንብታኡል። ሰሞኑንን ባራያ አላማጣ ሲካሄድ የቆየውን የተኩስ ልውውጥ ተከትሎ የትግራይ ሃይሎች “አሁን አላማጣ [ከተማ] ሊገቡ ሦስት ኪሎ ሜትር ነው የቀራቸው” ሲሉ የወረዳው ዋና አስተዳዳሪው አቶ ሞላ አስታወቁ። “የአካባቢው ሚሊሻና በትግራይ ሃይል መካከል ያለው ኃይል ባለመመጣጠኑ ምክንያት ሚሊሺያው አፈግፍጎ ተኩስ አቁሟል” ብለዋል።
“የአማራና የትግሬ ህብረት አስፈላጊ ነው። ስራም ጀምረዋል” በሚል በስፋት በሚነገርበት በአሁኑ ወቅት የትግራይ ሃይሎች አንዳንድ ቀበሌዎችን መቆጣጠራቸውን የራያ አላማጣ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሞላ የተናገሩት ለቢቢሲ ነው። “መከላከያው ትንኮሳ እንዲፈጠር አልፈለገም፤ ‘እባካችሁ’ እያለ እንደ ልመና ነው የያዘው። እየተጠየቁ ያለው እንደ ግዴታ አይደለም። እነሱ ግን ኃይላቸውን እያጠናከሩ እያስገቡ ነው ያለው። እኛም በተለይ በትናንትናው ዕለት ጋርጃሌ ከተማ ሊይዙብን ስለሆነ የምንችለውን ኃይሉን በሙሉ አሟጠን ብዙ ሞከርን፤ አልተቻለም” በማለት ስለ ሁኔታው አስረድተዋል።
“መከላከያው ትንኮሳ እንዲፈጠር አልፈለገም፤ ‘እባካችሁ’ እያለ እንደ ልመና ነው የያዘው። እየተጠየቁ ያለው እንደ ግዴታ አይደለም። እነሱ ግን ኃይላቸውን እያጠናከሩ እያስገቡ ነው ያለው። እኛም በተለይ በትናንትናው ዕለት ጋርጃሌ ከተማ ሊይዙብን ስለሆነ የምንችለውን ኃይሉን በሙሉ አሟጠን ብዙ ሞከርን፤ አልተቻለም” ብለዋል።
ከሁለቱም ወገን ክስ የሚሰማበት ይህ ውጊያ የላሊበላ ከተማ አፍንጫ ስር መጠጋቱ ቢገለጽም ከመንግስት ወገን የተባለ ነገር የለም። የአማራ ክልልም ቀደም ሲል ለትግራይ ክልል ከሰጠው ምላሽ በስተቀር ደግሞ ያነሳው ነገር ይህ እስከተጻፈበት ሰዓት ድረስ አልተሰማም።
የማራ ክልል ” በውክልና ክልሉን የማፈራረስ ተልዕኮ ያነገቡ ” በሚል በተፈረጁ፣ ራሳቸውን ግን የፋኖ ሃይል በሚል የሚጠሩ አካላት በክፈተቱት ጦርነት እየተተራመሰ ያለው የአማራ ክልል ወደ ሙሉ ወረራ ሊሸጋገር እንደሚችል በርካቶች ስጋታቸውን ሲገልጹ ሰንብተዋል።
በቅርቡ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ከትግራይ ተወካዮች ጋር ሲወያዩ ” ጦርነት ለማንሳት የሚፈልጉ አሉ። ምክሯቸው” ሲሉ ደጋግመው መናገራቸው ይታወሳል። በትግራይ ቁጥሩ አንድ ሚሊዮን የሚጠጋ ህይወት በጦርነቱ ማለፉንና ከፍተኛ የቁስ ሃብት መውደሙ አይዘነጋም።
በአማራ ክልልና በትግራይ መካከል ያሉ የይዞታ ይገባኛል ጥያቄዎች የተፈናቀሉ እንዲመለሱ ከተደረገ በሁዋላ በሂደት በህዝበ ውሳኔ ዘላቂ መፍትሄ እንዲበጅለት የመንግስት ፍላጎት እንደሆነ፣ ለዚህም ተግባራዊነት ከሁለቱም ክልሎች የተውጣጣ ኮሚቴ ተቋቁሞ ስራ መጀመሩ መገለጹ ይታወሳል። ተደጋጋሚ ውይይቶች መደረጋቸውን በዜና ተዘግቧል።
በወልቃይትና ጸገዴ ሁመራና ራያ ጉዳይ ምንም ዓይነት ድርድር ሊኖር እንደማይችል ደጋግሞ ያመለከተው ትህነግ ከአማራ ሃይሎች ጋር አብሮ ለመስራት ውስጥ ውስጡን ከጎጃም ሃይሎች ጋር መስማማቱን የሚከታተሉ ” ስምምነቱ ራያ፣ ወልቃይት ጠገዴን ሁመራን መልሶ ለመስጠት የተደረገ ነው? ” ሲሉ አማራ ክልል እርስ በርሱ የሚበታትን ስልት ነውና ከወዲሁ ጥንቃቄ ያሻል” ሲሉ ይመክራሉ። ዳግም ግጭትም ምንም ስለማይፈይድ የህዝብ ለህዝብ ግንኙነትን በማጠንከር ሰላማዊ መፍትሄ እንደሚሻል ይመክራሉ።
ይህ በንዲህ እንዳለ ነው አላማጣን ለመያዝ የትግራይ ሃይሎች በሶስት ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ መሆናቸውን አስተዳደሩ ያስታወቀው። ቢቢሲ ሁለቱም ወገኖች አነጋግሮ የሚከተለውን ዘግቧል።
በራያ አላማጣ ወረዳ ከቅዳሜ ጀምሮ ለቀናት የዘለቀ የተኩስ ልውውጥ መደረጉ ተገለጸ
የአማራ እና ትግራይ ክልሎች ከሚወዛገቡባቸው የራያ አካባቢዎች አንዱ በሆነው ራያ አላማጣ ወረዳ “የህወሓት ኃይሎች በከፈቱት ጥቃት” ከቅዳሜ እስከ ዛሬ የቆየ የተኩስ ልውውጥ መደረጉን የአካባቢው ባለሥልጣናት እና ነዋሪዎች ሲናገሩ፣ የደቡባዊ ትግራይ ዞን በበኩሉ ግጭት የተፈጠረው ታጣቂዎች በትግራይ ሚሊሻዎች ላይ ተኩስ በመክፈታቸው መሆኑን ገልጿል።
ከየካቲት ወር ጀምሮ በተደጋጋሚ የተኩስ ልውውጥ እየተደረገባቸው ካሉት የራያ ወረዳዎች አንዱ በሆነ ራያ አላማጣ የተከስ ልውውጡ በድጋሚ ያገረሸው ባለፈው ቅዳሜ ሚያዝያ 5/2016 ዓ.ም. ከቀኑ አምስት ሰዓት ገደማ ጀምሮ መሆነን የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሞላ ደርበው እና የአላማጣ ከተማ ከንቲባ አቶ ኃይሉ አበራ ለቢቢሲ ተናግረዋል።
ባለሥልጣናቱ “የህወሓት ኃይሎች” በማለት የሚጠሯቸው ታጣቂዎች፤ ተኩስ የከፈቱት በወረዳው አዲስ ብርሃን (በቀድሞ ስሙ ላዕላይ ድዩ) በተባለ ቀበሌ በኩል መሆኑን ገልጸዋል። ቅዳሜ፤ የነበረው ተኩስ እሁድም ቀጥሎ እንደዋለ እና ዛሬ [ሰኞ] ጠዋትም የተኩስ ልውውጥ ሲደረግ እንደነበር የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሞላ እና አንድ ነዋሪ ተናግረዋል።
በትግራይ ክልል የደቡባዊ ትግራይ ዞን ዋና አስተዳዳሪ የሆኑት አቶ ሀፍቱ ኪሮስ፤ ቅዳሜ እና እሁድ የፕሪቶሪያ ስምምነት እንዲተገበር የሚጠይቁ የራያ አካባቢ ተፈናቃዮች “ረጅም ርቀት በእግራቸው በመጓዝ” ሰልፍ ማድረጋቸውን አስታውሰዋል። ከመሆኒ እና ከማይጨው ከተሞች በመነሳት የተደረጉት ሰልፎች “የመከላከያ ሠራዊት ኬላ እስከሚገኝባቸው አካባቢዎች” የተደረጉ መሆናቸውን ጠቅሰዋል።
አቶ ሀፍቱ፤ “ድምጻችንን እያሰማን ባለንበት ወቅት ታጣቂዎች፤ ታኦ ከሚባል አካባቢ ተሰባስበው የእኛ ሚሊሻዎች ወዳሉበት አካባቢ [መጥተው] ለተኩስ የተጋበዙበት ሁኔታ ተፈጠረ” ሲሉ በሁለቱ አካላት መካከል ለተደረገው የተኩስ ልውውጥ ምክንያት የሆነውን ክስተት ጠቅሰዋል።
ይህንን ተከትሎ “ግጭቶች” መፈጠራቸውን የሚናገሩት የደቡባዊ ትግራይ ዞን ዋና አስተዳዳሪ፤ “ከእኛ ሚሊሻዎች ጋር ግጭት ተፈጠረ፤ [ከእኛ በኩል የነበሩት] ሚሊሻ እና ፖሊስ ናቸው። ሌላ ምንም ሌላ ዓላማ የነበረው አይደለም” ብለዋል።
የዚህን ተቃራኒ የሚናገሩት የራያ አላማጣ ባለሥልጣናት በበኩላቸው፤ ተኩስ የተከፈተው “አርሚ 24” ከተባለ የህወሓት የሠራዊት ክፍል ውስጥ “ሦስት ክፍለ ጦሮች” በአካባቢው ላይ ተሰማርተው እንደሆነ ገልጸዋል። የአላማጣ ከንቲባ አቶ ኃይሉ በበኩላቸው አካባቢው ላይ የተሰማሩት “አክሱም፣ አልጋነሽ እና ዮሐንስ ክፍለ ጦሮች” መሆናቸውን ተናግረዋል።
የወረዳው ዋና አስተዳዳሪው አቶ ሞላ በበኩላቸው፤ “ሦስት ክፍለ ጦር ይዞ እኛ ላይ ኦፕሬሽን እያደረገ ያለው አርሚ 24 ነው። [አርሚ] 44 እና 24 ነበሩ፤ በታች በኩል ያለው አርሚ 44 በባላ [ወረዳ] በኩል ምንም አልተጠጋም። አርሚ 24 ግን አክሱም ክፍለጦር ከእኛ ሚሊሻ ጋር እየተጋጨ ነው” ብለዋል።
- የኢትዮጵያ እና ኬንያ አትሌቶች ሆን ብለው ቻይናዊ ሯጭ እንዲያሸንፍ በማድረግ ተከሰሱከ 7 ሰአት በፊት
- ወደ ባንኮች ያዘዋወሩትን ገንዘብ መመለስ ባለመቻላቸው አጣብቂኝ ውስጥ የገቡት ተማሪዎች15 ሚያዚያ 2024
- የሶማሊያ የባሕር ላይ ወንበዴዎች መርከብ ማስለቀቂያ 5 ሚሊዮን ዶላር ተቀበልን አሉከ 8 ሰአት በፊት
ተኩስ የከፈተው ከባድ መሳሪያዎችን በመጠቀም መሆኑንም ባለሥልጣናቱ ገልፀዋል።
የአላማጣ ከንቲባ አቶ ኃይሉ፤ ታጣቂዎች “ብሬል፣ ዲሽቃ እና ስናይፐር” መጠቀማቸውን የተናገሩ ሲሆን፣ የወረዳው ዋና አስተዳዳሪው አቶ ሞላም “ዲሽቃ” በተባለው የቡድን መሳሪያ ተኩስ መከፈቱን ተናግረዋል። አንድ ነዋሪ በበኩላቸው ዛሬ አራት ሰዓት ገደማ ላይ “የዲሽቃ እና መትረየስ” ተኩስ ድምፅ መስማታቸውን አስረድተዋል።
የደቡባዊ ትግራይ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሀፍቱ ግን ይህንን አስተባብለዋል። “ይህ ነገር በሰላማዊ [መንገድ] ይፈታ እያልን ባለንበት ሰዓት፤ ሌላ ኃይል ልንጠቀም የሚያስችለን ምንም ምክንያት የለም” ብለዋል። እንደ ዲሽቃ ያሉት የቡድን መሳሪያዎች ጥቅም ላይ የዋሉት በተቃራኒ ወገን በሚገኙት የአካባቢው ታጣቂዎች መሆኑንም ተናግረዋል።
የራያ አላማጣ ባለሥልጣናት እና ነዋሪዎች፤ ከትግራይ ክልል መጥተዋል የሚሏቸው ታጣቂዎች፤ አዲስ ብርሃን የተባለውን ቀበሌ መቆጣጠራቸውን የተናገሩ ሲሆን፣ በዛሬው ዕለት ደግሞ “ጋርጃሌ” የተባለ አካባቢ መያዙን ጠቅሰዋል።
የራያ አላማጣ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሞላ፤ “መከላከያው ትንኮሳ እንዲፈጠር አልፈለገም፤ ‘እባካችሁ’ እያለ እንደ ልመና ነው የያዘው። እየተጠየቁ ያለው እንደ ግዴታ አይደለም። እነሱ ግን ኃይላቸውን እያጠናከሩ እያስገቡ ነው ያለው። እኛም በተለይ በትናንትናው ዕለት ጋርጃሌ ከተማ ሊይዙብን ስለሆነ የምንችለውን ኃይሉን በሙሉ አሟጠን ብዙ ሞከርን፤ አልተቻለም” ብለዋል።
“አሁን አላማጣ [ከተማ] ሊገቡ ሦስት ኪሎ ሜትር ነው የቀራቸው” ያሉት ዋና አስተዳዳሪው፤ የአካባቢው ሚሊሻ ያለው “ኃይል ባለመመጣጠኑ ምክንያት አፈግፍጎ ተኩስ መቆሙን” ገልፀዋል።
ከቅዳሜ ዕለት ጀምሮ በነበረው የተኩስ ልውውጥ የአንድ ሰው ሕይወቱ ሲያልፍ፤ ቁጥራቸው በውል ያልታወቀ ሰዎች መቁሰላቸውን ባለሥልጣናቱ እና ነዋሪዎች ተናግረዋል። ሕይወቱ ያለፈው ግለሰብ “ሚሊሻ” እንደሆነ አንድ የአካባቢው ነዋሪ ለቢቢሲ ተናግረዋል።
የደቡባዊ ትግራይ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሀፍቱ፤ ቅዳሜ ዕለት “ተከፍቶብናል” ባሉት ተኩስ የተጎዳ ሰው ስለመኖሩ ለቀረበላቸው ጥያቄ “በዚህ ጉዳይ ላይ ብዙም አስተያየት ባልሰጥ ደስ ይለኛል” የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።
የሰሜን ኢትዮጵያው ጦርነት መቀስቀሱን ተከትሎ በአማራ ክልል ስር የገቡት አወዛጋቢ አካባቢዎች ጉዳይ መፍትሔ የሚያገኘው በሕዝበ ውሳኔ እንደሆነ የፌደራል መንግሥት መግለፁ ይታወሳል። ጉዳዩን ለመፍታትም ከፌደራል መንግሥት እንዲሁም ሁለቱ ክልሎች ከፍተኛ አመራሮች ያሉበት ዐቢይ ኮሚቴ ሥራ ላይ መሆኑን የፌደራል መንግሥት አስታውቆ ነበር።
ከሁለት ሳምንት በፊት ጋዜጣዊ መግለጫ የሰጡት የመንግሥት ኮሚዩኒኬሽን ሚኒስትር ዶ/ር ለገሰ ቱሉ፤ “በአማራ አዋሳኝ አካባቢዎች” ላይ “በትግራይ በኩል” የሚታየው “አዝማሚያ”፤ የፕሪቶሪያውን ስምምነት የሚጥስ” እንደሆነ ተናግረው ነበር።
ዶ/ር ለገሰ፤ “ወሰንን በኃይል እናስከብራለን” የሚል አካሄድ “የትግራይ ሕዝብን ለሌላኛው ዙር ስቃይ እና እንግልት የሚዳርግ ነው” ሲሉም በዚህ መግለጫቸው አሳስበው ነበር።