መንግሥት የፋይናንስ ተደራሽነትና አካታችነትን ለማስፋት እየሰራ መሆኑን የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሺዴ ተናገሩ።የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በበኩሉ በምስረታ ላይ የሚገኙ ባንኮች በስድስት ወራት ውስጥ 500 ሚሊዮን ብር የተከፈለ ካፒታል እንዲያስመዝግቡ አሳስቧል።
በኢትዮጵያ የመጀመሪያው ሙሉ በሙሉ ከወለድ ነጻ አገልግሎት የሚሰጠው ዘምዘም ባንክ ስራ መጀመርን አስመልክቶ አቶ አህመድ ሺዴ ከአገራዊ ለውጡ በኋላ የፋይናንስ ተደራሽነትና አካታችነት ለማስፋት በመሰራት ላይ ነው ብለዋል።
በዚህም ከወለድ ነጻ የባንክ አገልግሎት ለውጡን ተከትሎ በተካሄዱት ሪፎርሞችና ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በሰጡት አመራር ወደ ሥራ መግባቱን ተናግረዋል።የሙስሊም ማህበረሰብ ሲያነሳው የነበረው በባንኩ ምስረታ ምላሽ ማግኘቱን ሚኒስትሩ አመልክተዋል።
ባንኩ ፍትሃዊ የልማት ተጠቃሚነት ከማረጋገጡም በላይ፤ በአገሪቱ ኢኮኖሚ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ብለዋል።የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንከ ገዥ ዶክተር ይናገር ደሴ በበኩላቸው የፋይናንስ ተደራሽነትን ለማስፋት በአገሪቱ ውስጥ ያሉትን የባንኮች አቅም ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑን አስታውቀዋል።
ባለፉት ሶስት ዓመታት የአገሪቱን ኢኮኖሚ ለማሳደግ አስተዋጽኦ ያላቸው በርካታ ማሻሻያዎች መደረጋቸውን ጠቁመዋል።በዚህም በዝቅተኛ ደረጃ ላይ የሚገኘውን ዘርፍ ለማሳደግ ባንኮች አቅም እንዲያጎለብቱ፣ ከጎረቤት አገሮች ባንኮች ጋር ጠንካራና ተፎካካሪ እንዲሆኑ ለማድረግ ፍላጎት እንዳለ ገዢው አመልክዋል።
በአገሪቱ ያሉ ባንኮች ራሳቸውን በቴክኖሎጂ፣ በሰው ኃይል፣ በመሰረተ ልማትና በካፒታል እንዲያሳድጉ አሳስበዋል።በአገሪቱ የፋይናንስ ተደራሽነበት በዝቅተኛ ደረጃ ላይ እንደሚገኝና በተለይ በገጠር ተደራሽነቱን ለማሻሻል እየተሰራ ይገኛል ብለዋል።
የፋይናንስ ተደራሽነት ለማስፋት ባንኮች በአቅምም ሆነ በብዛት ወደ ኢኮኖሚው ለማስገባት ድጋፍ እየተደረገ መሆኑንም አስረድተዋል።ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ከወለድ ነጻ ባንኮች እንዲፈጠሩ በሰጡት አቅጣጫ መሰረት ባንኩ በተለይ የፋይናንስ አገልግሎት ባልተዳረሰባቸው የገጠር አካባቢዎች ለማደረስ እየሰራ መሆኑን ጠቁመዋል።
ባንኩ በተለይ በእምነት ምክንያት የባንክ አገልግሎት ተጠቃሚ ያልሆኑ ዜጎችን ተጠቃሚ እንደሚያደርግ እምነታቸውን መሆኑን ዶክተር ይናገር ገልጸዋል።በአገሪቱ በምስረታ ላይ የሚገኙ ባንኮች በስድስት ወራት ውስጥ የተፈቀደ ካፒታላቸው መጠን 500 ሚሊዮን ብር አድርገው እንዲመዘገቡ ገዢው አሳስበዋል።
ይህንን ካፒታል ካላሟሉ ግን መመስረቻ ካፒታላቸው አምስት ቢሊዮን ብር እንደሚሆን ገልጸዋል።በአሁኑ ወቅት በምስረታ ላይ የሚገኙት 16 ያህል ባንኮች መስፈርቶችን በሟሟላት ወደ ሥራ እንዲገቡ ዶክተር ይናገር አስገንዝበዋል።
የዘምዘም ባንክ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ወይዘሮ መሊካ በድሪ እንዳሉት ባንኩ በአገሪቱ የፋይናንስ ዘርፍ አስተዋጽኦ ለመወጣትና አማራጭ የፋይናንስ አገልግሎት ለመስጠት የተቋቋመ ነው።በ876 ሚሊዮን ብር የተከፈለ ካፒታልና 1 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር የአክሲዮን ሽያጭ ያካሄደ ሲሆን፤ 11 ሺህ ባለ አክሲዮኖች አሉት ብለዋል።የሸሪያ ህግን የተከተለና ሁሉን አቀፍ የባንክ አገልገሎት በመስጠት በኢኮኖሚ ውስጥ ድርሻውን ለመወጣት እንደሚሰራም ወይዘሮ መሊካ ተናግረዋል።(ኢዜአ)
- አፍሪቃ ህብረት ምን አሰጋውና “ገንዘቤን ወደ ሌላ አገር ለማዛወር እያሰብኩ ነው” ሲል ተንሿከከ፤ የጾምና የፍስክ ዜናዎችባንኩ የክፍያ ሰነድ ቀረበለት። ማጣሪያ ጥያቄ ለህብረቱ አቀረበ። ሃሰት ሆኖ ተገኘና ፖሊስ ተጠርጣሪዎቹን ያዘ። ጉዳዩ ወደ ህግ አመራ።… Read more: አፍሪቃ ህብረት ምን አሰጋውና “ገንዘቤን ወደ ሌላ አገር ለማዛወር እያሰብኩ ነው” ሲል ተንሿከከ፤ የጾምና የፍስክ ዜናዎች
- የኢትዮጵያ ኤልክትሪክ ኃይል 300 ቢሊዮን ብር የንግድ ባንክ ዕዳ አለብኝ አለ፤ ዕዳውና የክፍያው ጫና እንደከበደውም አስታውቋልየኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከንግድ ባንክ 300 ቢሊዮን ብር ዕዳ እንዳለበት ተገለጸ። የዕዳ ጫናውን ለማቃለል የባንክ ወልዱም ጭምር ተፅእኖ… Read more: የኢትዮጵያ ኤልክትሪክ ኃይል 300 ቢሊዮን ብር የንግድ ባንክ ዕዳ አለብኝ አለ፤ ዕዳውና የክፍያው ጫና እንደከበደውም አስታውቋል
- ዋና ዋና የሽግግር ፍትህ ፖሊሲ ይዘቶች – ሲጨመቁመግቢያ ሽግግር ፍትህ ጉልህ የመብት ጥሰቶች በተፈፀመባቸው ሀገራት ተጠያቂነትን ለማስፈን እና ተበዳዮችን ለመካስ ጥቅም ላይ ሲውል ቆይቷል፡፡ በሀገራችንም… Read more: ዋና ዋና የሽግግር ፍትህ ፖሊሲ ይዘቶች – ሲጨመቁ
- “የአማራ ክልል ሚሊሻዎች ትጥቅ ይፍቱ በሚል የሚሰራጩ መረጃዎች ‘ባልበላውም ጭሬ ላፍሰው’ ከሚል ቅዠት የተወለደ ቅጥፈት ነው”“የሚሊሻ ኀይሉን በተመለከተ የሚዘዋወረው መረጃ ፍጹም መሠረተ ቢስ ነው” ሲሉ ኮሎኔል ግርማ ገሰሰ አስታወቁ። “ቅጥፈት ነው” ያሉትና በፕሬዚዳንቱ… Read more: “የአማራ ክልል ሚሊሻዎች ትጥቅ ይፍቱ በሚል የሚሰራጩ መረጃዎች ‘ባልበላውም ጭሬ ላፍሰው’ ከሚል ቅዠት የተወለደ ቅጥፈት ነው”
- “የህዝባችንን ድምጽ የሚቀማና የሚያፍን የ’አማራ ስብስብ’ ለአማራ ክልል ተግዳሮት ሆኗል… ትህነግ ዘርፎ እያጋጋዘ ነው” አብን“የትግራይ ተወላጆች ትህነግ ለፈጸመው ወረራ፣ ዘረፋ፣ ማፈናቀልና የግድያ ተግባራት የተቀናጀ የፖለቲካና የሚዲያ ድጋፍ ሰጥተዋል። በተለይም በትግራይ ክልል መቀሌ… Read more: “የህዝባችንን ድምጽ የሚቀማና የሚያፍን የ’አማራ ስብስብ’ ለአማራ ክልል ተግዳሮት ሆኗል… ትህነግ ዘርፎ እያጋጋዘ ነው” አብን