መተከል – ታጠቀው ጫካ የነበሩ “ዱር በቃን” ብለው ከነትጥቃቸው ገቡ

በመተከል ዞን ዳንጉር ወረዳ ታጥቀው ሲንቀሳቀሱ የነበሩ 90 ታጣቂዎች የመንግስትን የሰላም ጥሪ በመቀበል ከእነሙሉ ትጥቃቸው ተመለሱ፤ አቀባበልም ተደጎርላቸዋል።

በጦርነትና ግጭት ከመጠፋፋት ውጭ ምንም አይነት መፍትሄ አለመኖሩን በመረዳት መንግስት ያቀረበውን ጥሪ በመቀበል 90 የሚሆኑት ከእነሙሉ ትጥቃቸው የተመለሱ ሲሆን የቡድንና የነፍስ ወከፍ መሳሪያዎችን በመያዝ ነው።

በዞኑ ውስጥ በዳንጉርና ጉባ ወረዳዎች አዋሳኝ አካባቢዎች ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ታጣቂዎች ወደ ሰላም ሲመለሱ የግልገል በለስ ከተማ የሀገር ሽማግሌዎችና ከፍተኛ አመራሮች አቀባበል አድርገውላቸዋል።

በፕሮግራሙ ላይ የተገኙት የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ትምህርት ቢሮ ሃላፊ አቶ ቢኒያም መንገሻ እንደገለጹት መንግስት የዜጎችን ደህንነት ከማስጠበቅ ባለፈ በቀጠናው ዘላቂ ሰላምን በማስፈን ወደ ልማት ለመግባት ያቀረበውን ሰላም በመቀበል ለተመለሱ አካላት ወደ መደበኛ ስራቸው እንዲገቡ በትኩረት እንደሚሰራ ተገልጿል።

የመተከል ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ለሜሳ ዋውያ በበኩላቸው የሰላምን አማራጭ በመጠቀም ወደ ሰላም የተመለሱ ወገኖችን በማመስገን እነዚህ አካላት ወደ ኑሯቸው እንዲመለሱና ወደ ልማት ለማስገባት ይሰራል ብለዋል።

እነዚህን አካላት ወደ ሰላም ለመመስ ከሀገር መከላከያ ሰራዊት በተጨማሪ የሀገር ሽማግሌዎች ጉልህ ሚና ተጫውተዋል።

በቀጠናው የሀገር መከላከያ ሰራዊት እያካሄደ ባለው ህግ የማስከበር ተግባር ወደ ሰላም መመለሱ ይታወቃል ሲል የዞኑ ኮምንኬሽን ዘግቧል።

“የሞተው ባልሽ ገዳዩ ወንድምሽ፣ሀዘንሽ ቅጥ አጣ ከቤትሽ አልወጣ”
የሞተው ባልሽ ገዳዩ ወንድምሽ (ሀዘንሽ ቅጥ አጣ ከቤትሽ አልወጣ) የሚለው የቆየ ተረት ልብን የሚያደማ ኩነትን ማሳያ ነው። እቺ መከረኛ ሚስት ባልዋ በእናቷ ልጅ ወንድሟ ተገደለ። ሟች ባል፣ ገዳይ ወንድም … ኢህአፓ "ሃይማኖት …
እንደ ሱዳን የመሆን ምኞትና ጥድፊያ – የነጻ አውጪ ጋጋታ
በሱዳን ኮሽ ባለ ቁጥር " መንግስት ይናድ" እያሉ አደባባይ ወጥተው ጎማ የሚያነዱ ዛሬ ከስመዋል። ኮሽ ባለ ቁጥር ተተኪ ሳይዘጋጅላቸው መንግስታቸውን የናጡና የነቀነቁ ዛሬ የጸጸት ጊዜ ማግነት አልቻሉም። ተሰደዋል። ወይም የመንደር ለመንደር ሌቦች …
ኦቪድ ግሩፕ በአገር ውስጥ፣ አሜሪካ፣ ጀርመንና እስራኤል ስሜን አጠፉ ባላቸው ሚዲያና ግለሰቦች ላይ ክስ መሰረትኩ አለ
"ድርጅታችን ኦቪድ ግሩፕ በሀሰተኛ የመረጃ እና በስም ማጥፋት በተሳተፉ አካላት ላይ ክስ መስርቷል" ሲል በላከልን መግለጫ አመልክቷል። የድርጅቱን ዓላማ፣ መርህና ራዕይ እንዲሉም ያከናወናቸውን ተግባራት አስረድቶ " ስሜ ጠፍቷል" ሲል ክስ መመስረቱን ገልጿል። …
“ሀገር ወዳድነት፣ ማንበብ፣ ማሰብና ማንሰላሰል እንዲሁም ምክንያታዊነት የዚያ ዘመን በጎ ጎኖች ነበሩ”
ትናንት ከሀገር ፍቅር እና ደመ ሞቃትነት የተነሳ አንድ ትውልድ በሚባል መልኩ ዋጋ ከፍሏል። ከዚያ መማር የዚህ ትውልድ የቤት ሥራ ነው፡፡ ሀገርን መጠበቅ፣ ሥልጣኔን ማስቀጠል እና ውስብስብ የኾነውን ዓለም ተረድተው መውጫ ብልሃት የሚያመነጩ …
See also  የሚኒስትሮች ምክር ቤት በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳለፈ

Leave a Reply