ስማቸውን ካሰራጩት ደብዳቤ ግርጌ የዘረዘሩ ሰላሳ አምስት የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች በመጪው አዲስ ዓመት የ”ሰላም ጥሪ ” ሲሉ ባሰራጩት ጽሁፍ መንግስት ሁሉን አቀፍ መድረክ እንዲያመቻች ጠየቁ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ እርቅ ኮሚሽን ሲያሰባስብ የቆየውን ግብአት አደራጅቶ በመጪ አዲስ ዓመት ሁሉ አቀፍ የዕርቅ ማድረክ እንዲያዘጋጅ ማስታወቁን ተከትሎ የቀረበው ጥሪ ነው።
በሽግግር ፍትህ ፖሊሲ እንዲታዩ ዕቅድ ተይዞባቸው ከአራት ወረዳዎች፣ እንዲሁም በውልቃይት ጠገዴ ባለው የባልቤትነት ጥያቄ የተነሳ ከሃሜት ለመዳን ካለመከናወኑ በቀር በመላው አገሪቱ ግብዓት በመስብሰብ የትነተና ስራ ብቻ እንደቀረ ባለፈው ሳምት ኮሚቴው ማስታወቁ ይታወሳል። እርቅን ከፍትህ ጋር አስተሳስሮ አገሪቱን በየጊዜው ለውዝግብና እልቂት የሚዳርገውን ትርክት ለመቋጨት የተቋቋመው ኮሚሽን የተጋብር ስራውን በአዲሱ ዓመት ማግስት እንደሚያስጀምር የሚታወስ ነው።
ተጠያቂነትን ለማስፈን ፍትህ ሚኒስቴር
ኮሚቴው ” ለዘላቂ ሰላምና ለአገረ መንግስት ግንባታ የራሳቸዉ መሰረታዊ አስተዋፅኦ እንዳላቸዉና የሽግግር ፍትህ ዋነኛዉ ትኩረት ተፈፀሙ የሚባሉ ከፍተኛ የሰብአዊ መብት ጥሰቶች ላይ መሆኑንና በእነዚህ ሂደቶች ክስ የሚኖር መሆኑን በመግለፅ በአገራዊ ምክክር ላይ ግን በአብዛኛዉ ክስ የሌለ መሆኑ ልዩ ያደርጋቸዋል ሲሉ ከተቋማዊ አደረጃጀት አነፃርም የሽግግር ፍትህ በሁለት አይነት እንደሚደራጀና እነዚህም እዉነት ኮሚሽንና ፍርድ ቤት ላይ የሚተገበሩ ሲሆን አገራዊ ምክክር በአገራዊ ምክክር ኮሚቴ መሰል ቡድኖች እንደሚደራጅና በጥቅሉ አገራዊ ምክክር በሽግግር ፍትህ አማራጮች እንደ አንድ አማራጭ መካተቱንም አያይዘዉ አዉስተዋል” ሲል በጋዜጣ መግለጫው ወቅት መናገሩን ፍትህ ሚኒስቴር በገጹ አመልክቷል።
እነዚሁ ድርጅቶች ላቀረቡት ጥሪ የመንግስት ምላሽ ለጊዜው አልታወቀም። በኢትዮጵያ ህዝብ ሰላም እንዲሰፍን መናፈቅ የእለት ተዕለት ስራው ሆኗል። የዚያኑ መጠን ሚዲያዎችና ማህበራዊ አውዶች ምንጩ ከማይታወቅ መረጃ በተጨማሪ በተቀነባበረና በተናበበ የፈጥራ ዜና የአገሪቱን ሰላም በስፋት እያወኩ እንደሆነ በተደጋጋሚ እየተገለጸ ነው።
ድርጅቶቹ የጥላቻ ንግግርና የተዛቡ መረጃዎችን ማሰራጨት እንዲቆም፣ ህዝብን በጅምላ መፈረጅ አግባብ እንዳልሆነ ጨምርው ካነሱዋቸው አሳቦች በተጨማሪ በዋናነት ያነሷቸውን አሳቦች ከስር የመለከቱ። መግለጫቸውንም ያንብቡ።
- አገር አቀፍ የሰላም መድረክ ይመቻች
- ገለልተኛ ምርመራና ተጠያቂነት ይስፈን
- ፆታዊ ጥቃቶች ተገቢው ትኩረት ይሰጣቸው
- የተጋላጭ እና ግፉአን ጥበቃ ማዕቀፍ ይዘርጋ
- ሕዝባዊ ተሳትፎ ይረጋገጥ
- የቅድመ ግጭት መጠቆሚያ እና መከላከያ ስርዓት (Early warning System) ይኑር
- የሰብዓዊ ድጋፍ አቅርቦት ሳይስተጓጎል ይቀጥል
- የጥላቻ ንግግር እና የተዛቡ መረጃዎች ስርጭት ይቁም
- የሲቪክ ምኅዳሩ ጥበቃ ይደረግለት
- ባለድርሻ አካላት ለሰላም ግንባታ የበኩላቸውን ይወጡ ሲሉ ጥሪያቸውን አቅርበዋል። ጥሪያቸውን ዛሬ በአዲስ አበባ ካፒታል ሆቴል በሰጡት መግለጫም አመልክተዋል።
ድርጅቶቹ በአሳብ ተመሳሳይ ይዘት ይዞ በስፋት ሲሰራ ከቆየው ከአገር አቀፍ የምክክር መድረክ በተለየ አዲስ የምክክር መድረክ እንዲመቻች የጠየቁበትን ምክንያት ይፋ አላደረጉም። ድርጅቶቹ አብዛኞቹ በስም መኖራቸው ጭምር የማይታወቅና ቀደም ሲል ተዘግተው ወይም በህግ ገለልተኛ አይደላችሁም በሚል በር የተዘጋባቸውና ከለውጡ በሁዋላ ህልውናቸውን ዳግም የገኙ ድርጅቶች ናቸው። ዛሬ የተሰጠውን ሙሉ መግለጫ ከላይ ያንብቡ።
- አፍሪካ ህብረት ” የውጭ ምንዛሪ ሒሳቡን ወደ ሌላ ሀገር ሊያዘዋውር ነው” የሚለው ዜና ሃሰት መሆኑን አረጋግጠአፍሪካ ህብረት የውጭ ምንዛሬ አካውንቱን ወደ ሌላ አገር እንደሚያዘዋውር ተጠቅሶ በህብረቱ ስም የወጣው ዜና ሃሰት፣ ሆን ተብሎ የተቀነባበረ… Read more: አፍሪካ ህብረት ” የውጭ ምንዛሪ ሒሳቡን ወደ ሌላ ሀገር ሊያዘዋውር ነው” የሚለው ዜና ሃሰት መሆኑን አረጋግጠ
- አፍሪቃ ህብረት ምን አሰጋውና “ገንዘቤን ወደ ሌላ አገር ለማዛወር እያሰብኩ ነው” ሲል ተንሿከከ፤ የጾምና የፍስክ ዜናዎችባንኩ የክፍያ ሰነድ ቀረበለት። ማጣሪያ ጥያቄ ለህብረቱ አቀረበ። ሃሰት ሆኖ ተገኘና ፖሊስ ተጠርጣሪዎቹን ያዘ። ጉዳዩ ወደ ህግ አመራ።… Read more: አፍሪቃ ህብረት ምን አሰጋውና “ገንዘቤን ወደ ሌላ አገር ለማዛወር እያሰብኩ ነው” ሲል ተንሿከከ፤ የጾምና የፍስክ ዜናዎች
- የኢትዮጵያ ኤልክትሪክ ኃይል 300 ቢሊዮን ብር የንግድ ባንክ ዕዳ አለብኝ አለ፤ ዕዳውና የክፍያው ጫና እንደከበደውም አስታውቋልየኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከንግድ ባንክ 300 ቢሊዮን ብር ዕዳ እንዳለበት ተገለጸ። የዕዳ ጫናውን ለማቃለል የባንክ ወልዱም ጭምር ተፅእኖ… Read more: የኢትዮጵያ ኤልክትሪክ ኃይል 300 ቢሊዮን ብር የንግድ ባንክ ዕዳ አለብኝ አለ፤ ዕዳውና የክፍያው ጫና እንደከበደውም አስታውቋል
- “የአማራ ክልል ሚሊሻዎች ትጥቅ ይፍቱ በሚል የሚሰራጩ መረጃዎች ‘ባልበላውም ጭሬ ላፍሰው’ ከሚል ቅዠት የተወለደ ቅጥፈት ነው”“የሚሊሻ ኀይሉን በተመለከተ የሚዘዋወረው መረጃ ፍጹም መሠረተ ቢስ ነው” ሲሉ ኮሎኔል ግርማ ገሰሰ አስታወቁ። “ቅጥፈት ነው” ያሉትና በፕሬዚዳንቱ… Read more: “የአማራ ክልል ሚሊሻዎች ትጥቅ ይፍቱ በሚል የሚሰራጩ መረጃዎች ‘ባልበላውም ጭሬ ላፍሰው’ ከሚል ቅዠት የተወለደ ቅጥፈት ነው”
- “የህዝባችንን ድምጽ የሚቀማና የሚያፍን የ’አማራ ስብስብ’ ለአማራ ክልል ተግዳሮት ሆኗል… ትህነግ ዘርፎ እያጋጋዘ ነው” አብን“የትግራይ ተወላጆች ትህነግ ለፈጸመው ወረራ፣ ዘረፋ፣ ማፈናቀልና የግድያ ተግባራት የተቀናጀ የፖለቲካና የሚዲያ ድጋፍ ሰጥተዋል። በተለይም በትግራይ ክልል መቀሌ… Read more: “የህዝባችንን ድምጽ የሚቀማና የሚያፍን የ’አማራ ስብስብ’ ለአማራ ክልል ተግዳሮት ሆኗል… ትህነግ ዘርፎ እያጋጋዘ ነው” አብን