በእነ ጃዋር የህክምና ጥያቄ ጠቅላይ ፍርድ ቤት የሁሉንም ተከራካሪዎች ጥያቄ ውድቅ አደረገ፤ ቃሊቲ ሆነው ይታከማሉ፤

በእነ ጃዋር ጉዳይ ይግባኝ የቀረበለት የየቅላይ ፍርድ ቤት የክፍተኛውን ፍርድቤትና የአቃቤ ህግ ይግባኝ ውድቅ አድርጎ አዲስ ውሳኔ አሳለፈ። የፌደራል ማረሚያ ቢት ምክትል አስተዳዳሪ ታስረርው እንዲቀርቡ ታዘዘ።

“ሁከት በመቀስቀስና  ሕዝብን ከሕዝብ ለማጋጨት በመሞከር” በሚል ወንጀል ተጠርጥረው ክስ የተመሰረተባቸው የኦፌኮ አመራሮች  አዲስ በሚቋቋም የሐኪሞች ቡድን ቃሊቲ ሆነው እንዲታከሙ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት መወሰኑ ተሰማ።

አቶ ጀዋር መሐመድ፣ አቶ በቀለ ገርባና በተመሳሳይ ጭብጥ የተከሰሱት የረሃብ አድማ ማድረግ ጫና ለመፍጠር መሞከራቸውና የጤናቸውን ሁኔታ ደግሞ በግል ሃኪሞቻቸው መከታተል እንዲችሉ እንዲደረግ መጠየቃቸው የሚታወስ ነው። 

እነ ጃዋር በግል ሐኪሞቻቸዉ ይታከሙ ወይስ በመንግስት ሐኪሞች የሚለዉ ልዩነት ሰፊ መከራከሪያ ሆኖ ቆይቶ ነበር። ዛሬ ይፋ እንደሆነው በጉዳዩ ይግባኝ የቀረበለት ጠቅላይ ፍርድ ቤት፣የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤትን ዉሳኔና ዉሳኔዉን የተቃወመዉን የጠቅላይ አቃቤ ሕግን ይግባኝ ዉድቅ አድርጎ አዲስ ዉሳኔ አሳልፏል።

በዉሳኔዉ መሠረት የሐኪሞች ቡድን ተቃቁሞ፣ ቡድኑ ተከሳሾችን እታሰሩበት ቃሊቲ ወሕኒ ቤት ድረስ እየሔደ ያክማል።በሌላ በኩል ከተከሳሾች ጠበቆች አንዱ እንዳስታወቁት የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት እስካሁን የሰጠውን ውሳኔ ወሕኒ ቤት ባለማክበሩ የፊታችን ሃሙስ የፌዴራሉ ማረሚያ ቤት ምክትል አስተዳዳሪ ታስረው እንዲቀርቡ አዟል።


See also  [አብይና ትግሬ ታረቁ - አብረው አማራን ሊያጠቁ] የአንገት በላይ ቁምጥና

1 Comment

  1. https://www.waitlistcheck.com/CT2561

    Jawar’s supporters are moving from Minnesota to Connecticut within USA to regroup and recuperate . The Deadline for free online application at the website https://www.waitlistcheck.com/CT2561 for refugees housing application for single , disabled or elderly refugees is this coming Thursday 02/25/2021.

    Hartford, the capital city of the Connecticut State in USA’s public housing authority is giving lottery condo housing applications for single or elderly or disabled foreign refugees to be put on the wait list paid by the USA government subsidized housing program with application accepted only until Thursday February the 25th 2021.

    https://www.waitlistcheck.com/CT2561

Leave a Reply