አሸባሪ የህወሃት ቡድን በራያና አዘቦ ”የለውጥ ደጋፊዎች ናችሁ” በሚል ንጹሃን ዜጎችን እየገደለ መሆኑን የራያ ራዩማ ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ ጽህፈት ቤትና የውጭ ግንኙነት ሀላፊ ጌታቸው ከበደ ገለጹ፡፡
ባላቸው ስጋት ምክንያት ከአስር ሺህ በላይ ነዋሪዎች ከቤት ንብረታቸው መፈናቀላቸውንም ገልጸዋል።
ኢዜአ የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ከትግራይ ክልል መልቀቅ ተከትሎ በራያ አካባቢ ያለው ወቅታዊ ሁኔታ ምን እንደሚመስል ከአቶ ጌታቸው ከበደ ቆይታ አድርጓል፡፡
የፌዴራል መንግስት በትግራይ ክልል የተናጠል የተኩስ ማቆም ውሴ መወሰኑን ተከትሎ አሸባሪ የህወሃት ቡድን ”የለውጥ ደጋፊ ናችሁ” በሚል ከፍተኛ ሰብዓዊ እና ቁሳዊ ጉዳት ማድረሱን አቶ ጌታቸው ከበደ ተናግረዋል፡፡
ቡድኑ ንጹሃንን እየገደለ፣ ቤትና ንብረቶችን በማውደም ራያ አዘቦ ተብሎ በሚታወቀው መሆኒ፣ መቻሬ፣ ጨርጨር እና ሓደ አልጋ በታባሉ አካባቢዎች በሰው ህይወትና በንብረት ላይ ከባድ ጉዳት ማድረሱን ተናግረዋል፡፡
ሽብርተኛ ቡድኑ ቀደም ሲል መከላከያ ወደ አካባቢው በገባበት ወቅት አቀባበል ያደረጉ፣ ስንቅ ያቀረቡ፣ ለሰራዊቱም የባህል ልብስ ያለበሱ ናቸው በሚል በሻይ መሸጥ የሚተዳደሩ፣ የባህል ልብስ የሚሰሩ፣ በጫማ ማጽዳት ስራ የተሰማሩ ደሃ ሰዎችን በግፍ በመግደል የጥፋት ስራዎችን መስራቱን አመላክተዋል፡፡
በዚህም በአካባቢው እየተፈጠረ ባለው ችግር ስጋት ምክንያት ከአስር ሺህ በላይ የሚቆጠሩ ነዋሪዎች መከላከያ ባለባቸው የራያ የገጠር እና የከተማ አካባቢዎች በርታህላ፣ ታኦ፣ ዳዩ፣ አላማጣ፣ እንዲሁም ራያ ቆቦ ከተማ ጭምር ተጠልለው ይገኛሉ ብለዋል፡፡
አሸባሪው የህወሃት ቡድን ”እናስተምራችዋለን” በሚል ሰበብ በርካታ ወጣቶችን በሲኖ ትራክ መኪና ጭነው በመውሰድ ኢ ሰብዓዊ ድርጊት እየፈጸሙባቸው መሆኑንም ተናግረዋል።
የለውጥ ደጋፊዎች ናችሁ በሚል የጊዜያዊ አስተዳደር አባላት እና የነዋሪዎች መኖሪያ የሆኑ ከአራት መቶ በላይ ቤቶችን መቃጠላቸውን ገልጸዋል።
በትግራይ ክልል መቀሌ እና በሌሎች ከተሞች ከጊዜያዊ አስተዳደሩ እና መከላከያን ተባብራችኋል ያላቸውን ንጹሐን ላይ ግድያ እየፈጸመ እንደሚገኝ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መረጃ ማጣሪያ ገልጿል።
- አፍሪቃ ህብረት ምን አሰጋውና “ገንዘቤን ወደ ሌላ አገር ለማዛወር እያሰብኩ ነው” ሲል ተንሿከከ፤ የጾምና የፍስክ ዜናዎችባንኩ የክፍያ ሰነድ ቀረበለት። ማጣሪያ ጥያቄ ለህብረቱ አቀረበ። ሃሰት ሆኖ ተገኘና ፖሊስ ተጠርጣሪዎቹን ያዘ። ጉዳዩ ወደ ህግ አመራ።… Read more: አፍሪቃ ህብረት ምን አሰጋውና “ገንዘቤን ወደ ሌላ አገር ለማዛወር እያሰብኩ ነው” ሲል ተንሿከከ፤ የጾምና የፍስክ ዜናዎች
- የኢትዮጵያ ኤልክትሪክ ኃይል 300 ቢሊዮን ብር የንግድ ባንክ ዕዳ አለብኝ አለ፤ ዕዳውና የክፍያው ጫና እንደከበደውም አስታውቋልየኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከንግድ ባንክ 300 ቢሊዮን ብር ዕዳ እንዳለበት ተገለጸ። የዕዳ ጫናውን ለማቃለል የባንክ ወልዱም ጭምር ተፅእኖ… Read more: የኢትዮጵያ ኤልክትሪክ ኃይል 300 ቢሊዮን ብር የንግድ ባንክ ዕዳ አለብኝ አለ፤ ዕዳውና የክፍያው ጫና እንደከበደውም አስታውቋል
- ዋና ዋና የሽግግር ፍትህ ፖሊሲ ይዘቶች – ሲጨመቁመግቢያ ሽግግር ፍትህ ጉልህ የመብት ጥሰቶች በተፈፀመባቸው ሀገራት ተጠያቂነትን ለማስፈን እና ተበዳዮችን ለመካስ ጥቅም ላይ ሲውል ቆይቷል፡፡ በሀገራችንም… Read more: ዋና ዋና የሽግግር ፍትህ ፖሊሲ ይዘቶች – ሲጨመቁ
- “የአማራ ክልል ሚሊሻዎች ትጥቅ ይፍቱ በሚል የሚሰራጩ መረጃዎች ‘ባልበላውም ጭሬ ላፍሰው’ ከሚል ቅዠት የተወለደ ቅጥፈት ነው”“የሚሊሻ ኀይሉን በተመለከተ የሚዘዋወረው መረጃ ፍጹም መሠረተ ቢስ ነው” ሲሉ ኮሎኔል ግርማ ገሰሰ አስታወቁ። “ቅጥፈት ነው” ያሉትና በፕሬዚዳንቱ… Read more: “የአማራ ክልል ሚሊሻዎች ትጥቅ ይፍቱ በሚል የሚሰራጩ መረጃዎች ‘ባልበላውም ጭሬ ላፍሰው’ ከሚል ቅዠት የተወለደ ቅጥፈት ነው”
- “የህዝባችንን ድምጽ የሚቀማና የሚያፍን የ’አማራ ስብስብ’ ለአማራ ክልል ተግዳሮት ሆኗል… ትህነግ ዘርፎ እያጋጋዘ ነው” አብን“የትግራይ ተወላጆች ትህነግ ለፈጸመው ወረራ፣ ዘረፋ፣ ማፈናቀልና የግድያ ተግባራት የተቀናጀ የፖለቲካና የሚዲያ ድጋፍ ሰጥተዋል። በተለይም በትግራይ ክልል መቀሌ… Read more: “የህዝባችንን ድምጽ የሚቀማና የሚያፍን የ’አማራ ስብስብ’ ለአማራ ክልል ተግዳሮት ሆኗል… ትህነግ ዘርፎ እያጋጋዘ ነው” አብን