የኢትዮጵያን ነዳጅና የተፈጥሮ ጋዝ ሀብት አቅም የሚያሳይ የጥናት ሰነድ ይፋ ሆነ


ኢትዮጵያ ያላትን የነዳጅ ሀብትና የተፈጥሮ ጋዝ አቅም የሚገልፀው የአዋጭነት ጥናት ሰነድ ዛሬ ይፋ ተደርጓል።

ጥናቱ ባለፉት አምስት ወራት በአሜሪካው ኔዘርላንድ ሲዌልና አሶሺዬት ካምፓኒ አማካኝነት የተከናወነ ሲሆ የጥናቱን ሰነድ ለማዕድን ሚኒሰቴር ሚኒስትር ኢንጂነር ታከለ ኡማ ተረክበዋል።

በመድረኩ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ብርቱካን አያኖ የሰነዱ መዘጋጀት የኢትዮጵያን ንግድና ኢቨንስትመን ለአለም ማህበረሰብ ይበልጥ በማስተዋወቅ ትልልቅ ኢንቨስትመንትን ለመሳብ የጎላ አበርክቶ እንደሚኖረው ጠቁመዋል።

ጥናቱ በአሜሪካ ካምፓኒ መደረጉን ያስታወሱት ሚኒስትር ዴኤታዋ ይህም የሁለቱን ሀገራት መልከ ብዙ ትብብር የሚያሳይ መሆኑን ጠቁመዋል።

የማዕድን ሚኒስትሩ ክቡር ኢንጂነር ታከለ ኡማ በበኩላቸው ሰነዱ ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ደረጃ በኢንቨስትመንት መስክ ከፍተኛ አቅም ያላቸውን ኩባንያዎች ለመጋበዝ ትልቅ ሚና እንደሚጫወት ገልጸዋል።

በዘርፉም የመንግስትን የመደራደሪያ አቅምን የሚያጎለብት ነው ብለዋል።

ሰነዱ የተፈጥሮ ጋዝና ድፍድፍ ነዳጅ የማልማት ሀገራዊ እቅዳችንን አንድ እርምጃ ያራመደ በትልቁ የመንግስትን ቁርጠኝነት የሚያሳይ የስራ ውጤት ነው ብለዋል። (ኢ ፕ ድ)

See also  ተከዜ - አዲሱ የትህነግ የድንጋይ ዘመን ዕቅድ - ኦቻ የአማራ ልዩ ሃይልን ወነጀለ

Leave a Reply