በወረራው ወቅት ዓለም አድሞ ኢትዮጵያ ላይ ባዘመታቸው ሚዲያዎች፣ ትህነግ ራሱ ባቋቋማቸው የማህበራዊ መገናኛዎችና ለትህነግ ተከፍሏቸው በሚሰሩና አሜሪካ፣ እንግሊዝና ጀርመን በከፈቷቸው የጥቅማቸው ማስከበሪያ ጣሚያዎች ያለ ከልካይ የቃላት ሚሳይል ሲረጩ የነበሩት አቶ ጌታቸው አሁንም ባለ ምነታ ምላስ መሆናቸው በማስረጃ እየተገለጸ ነው።
የትግራይን ወጣት፣ ሙት፣ ቁስለኛ፣ አካለ ጎዶሎነት ከዳረጉት በህይወት ያሉ አመራሮች መካከል አንዱና ዋናው እንደሆኑ የሚነገርላቸው አቶ ጌታቸውን ጨምሮ ድፍን የትህነግ አመራሮች ለፍርድ መቅረብና በትግራይ ህዝብ መዳኘት ይገባቸው እንደነበር በተደጋጋሚ አሁን ድርርስ የሚገልጹ አሉ።
ትህነግ በክህደት የጀመረው ጦርነት የትግራይን እናቶች ልጅና ጠዋሪ አልባ፣ በውጭ ሆነው ጦረንቱን ሲያግሙ ለነበሩ የሃብት ምንጭ ሆኖ የተገባደደው ጦርነት መጨረሻው ወደፊት ይፋ ከሚሆነው ዘግናኝ ኪሳራ በሁዋላ “በአድኑኝ” ጩኸት መጠናቀቁ ይታወሳል። ይህን ተከትሎ የትግራይ መሪ የሆኑት አቶ ጌታቸው ምድር ላይ ያልተሰሙትን የማቆሸሺያ ቃላቶች ሳይቀር ተጠቅመው ሲዛበቱባቸው በነበሩት ጠቅላይ ሚኒስትር ፊት ይቆማል የሚል ግምት አልነበረም።
“የካድሬን ባህሪና የሰውነት ደረጃ ማሳያ ሆነው ለቀጣዩ ትውልድ ማስተማሪያ ከሚሆኑት ወራዳዎች መካከል አቶ ጊታቸው አንዱ ናቸው። የፊልም ጠበብቶች በሰነድነት የሚቀመጥ ሙሉ ዶክመንታሪ ፊልም ሊሰሩ ይገባል” ሲሉ አቶ ደምሰው ሃይሉ የተናገሩትም ለዚሁ ይመስላል። ነውም።
በሂደት ከሃሰትና ከቅጥፈት ስብከት ጋር ተጋብተው ህሊናቸውን ያነጠፉት አቶ ጌታቸው ” ነገር በዓይን ይገባል” እንዲሉ ጸሃይ ቀርቶ በቂ ብርሃን በሌለበት አዳራሽ አይናቸውን በትልቅ የጠርሙስ መነጥር እየሸፈኑ ለህዝብ ሌላ፣ ለትግራይ ወጣቶችና አሁን ድረስ የትህነግ ፍቅር ለሚያንዘርዘራቸው የድንጋይ ዘመን አሳቢዎች ሌላ እያወሩ ነው።
አስፋው አብርሃ እስር እስራቸው እያለ በቃል በቃል ትርጉም ቪዲዮ እያመስካረና መረጃ እያደረገ ካቀርበው የአቶ ጌታቸው መንታ ምላስ አሁንም እንዳልዶለዶመ ለማሳያ ይህን ለማጋራት ወደድኩ። የትህነግ ፍቅር ለሚያንዘፈዘፋቸው አስተዋይነትን እየተመኘሁ፣ በትግራይ ህዝብ ማገዶነት ሲነገዱና ሃብት ሲያሰባስቡ ለነበሩ፣ አሁንም ፊታቸውን ቀይረው ገንዘብ ለቀማ ላይ ሙጭጭ ላሉ ቢያንስ አካለ ጎዶሎ ለሆኑት ምስኪኖች ሲሉ ወደ ቀላባቸው እንዲመለሱ ከሰሙ ምክሬን እለግሳለሁ። አስፋው ካዘጋጃቸው ውስጥ የሚከተለውን እዩልኝ። እውን አቶ ጌታቸው መሪ ናቸው? ሚሊዮኖች ደምና አስከሬን ላይ ቆመው ስለ እርቅና ምህረት የሚያወሩት በዚህ ልቡናቸው ነው? እንዲህ ባሉ ሰዎች የትግራይ ህዝብ ስንት ዓመት፣ ስንት ጊዜ ይታለላል? ለምን ያህል ዘመን ነው መቃብር የሚያየው? ከወዳጆቹና ጎረቤቶቹ ጋር ሆድና ጀርባ ሆኖ እንዲኖር የሚፈረድበት? እስከመቼስ ነው “እምቢ” የማይለው? እስከመቼ ነው ልጆቹን በትህነግ ጨርቅና ፕሮፓጋንዳ እየጠቀለለ የሚቀብረው? መቼ ነው የትግራይ ምሁራን ” በቃ” ብለው የማይነሱት? በትግራይ ህዝቡን ያደነዘዘውና ያሳወረው ምን ይሆን?
- አትሸወዱ! የትግራይ ደህንነት(Security) ከእጃችን አልወጣም። ያ ሲባል ግን መቼም ቢሆን ጦርነትን ምርጫ አናደርግም። በሆነ አጋጣሚ ጦርነት የግድ ከሆነና appetite ካለን ግን ማን ያግደናል? ሰራዊታችን እንደሆነ ከኛ ጋር ነው ያለው።
- ትጥቅ በመፍታትና መሳሪያ በማስረከቡ ዙሪያ ላይ ምንም መደናገር አያስፈልግም። እነሱ የፈለጉት ሌላ ነበር። የሆነው ሌላ ነው። በዚህ ዙሪያ ብዙ መናገር አልፈልግም -sensitive material ነው። እርግጥ በትጥቅ ማስፈታት ዙሪያ የሚሰሩ የቴሌቪዢን ፕሮግራሞችን ሲመለከቱ ስጋት የሚገባቸው አንዳንድ የኛ ሰዎች እንዳሉ አውቃለሁ።
- አሁን ለምሳሌ መንግስት ደብዳቤ ሲፅፍልን “የትግራይ አካታች ጊዜያዊ መንግስት” እያለ ነው የሚፅፍልን። ይሄ ለምን ሆነ? የትግራይ ጊዜያዊ መንግስት ለምን አልተባለም? ስንላቸው “አይ ካቢኔው ከበፊቱ የተቀየረ ለመሆኑ ለህዝብ ለማሳየት ነው” ይሉናል። ይሄ ደግሞ እኛን ይጠቅመናል እንጂ አይጎዳንም። እነሱ ይቺን ሲሉ ኦኮ “ትግራይ ውስጥ ምንም የተቀየረ ነገር የለም። ሁሉም ነገር በህወሐት እየተፈፀመ ነው” የሚለውን ትችት ከወዲሁ ለማስቀረት እንደ “ታኮ” ነው የሚጠቀሙባት። እውነታው ግን አሁን ያሉት የካቢኔው አባላት ያው በፊት የተመረጡት የመጀመሪያዎቹ ሰዎች ናቸው። ደብረፂዮን ብቻ ነው የተቀየረው። እሱንም እኔ ነኝ የተካሁት። እኔ ደሞ የህወሓት ስራአስፈፃሚ ነኝ።
- አሁን ለምሳሌ ዶ/ር አቢይንም ሆነ አቶ ኢሳያስን በጄኖሳይድ ወንጀል ለመክሰስ ጊዜውም ሆነ ሁኔታዎች ለኛ አይፈቅዱልንም። ሌላው ቀርቶ አሜሪካ እንኳን በትግራይ ህዝብ ላይ ጄኖሳይድ ተፈፅሟል ብላ ለመፈረጅ ጫፍ ከደረሰች በኋላ ግራ በሚገባ ሁኔታ ፍረጃውን ትታ ጭራሽ እኛንም በወንጀሉ ተጠያቂ እንደሆንን በመጥቀስ በቆቦና በጭና ወንጀል ፈፅማችኋል የሚል allegation ሰነዝራብናለች።
- ጌታቸው ንግግሩን የቀጠለው ማንኛውም የአንድ አገር ወንጀለኛ መሪ የዘገየውን ያህል ቢዘገይ ከመጠየቅ እንደማይድን ቻርለስ ቴለርንና ዑመር አልበሽርን እንደ ምሳሌ በመጥቀስ ነበር። በዚህ ንፅፅራዊ ማጣቀሻው ላይ ቻርለስ ቴለር በICC ከተከሰሰ ከ10 አመት በኋላ በወንጀሉ እንደተጠየቀ ጠቅሷል።
- ጌታቸው በዚህ ንግግሩ ላይ ይህ የተጠያቂነት ጉዳይ እንደሌሎቹ ወንጀለኞች ሁሉ 10 እና ከዛ በላይ አመታት መጓተት እንደሌለበት ጠቅሶ አሁን ባለው ነባራዊ እውነታ ምክንያት ግን የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደርም ሆነ ህወሓት የተጠያቂነትን ጉዳይ በአጀንዳነት አንስቶ ንቅናቄ መፍጠር ስለሚያዳግተው በአክቲቪዝሙ ላይ የሚሳተፉ የትግራይ አክቲቪስቶች አጀንዳውን ማስተጋባት እንዳለባቸው አሳስቧል።
- በንግግሩ መጨረሻ ላይ እነ ዶ/ር አቢይን ለመወንጀል በትጋት እንዲሰሩ ጥሪ ላደረገላቸው የትግራይ አክቲቪስቶች “ስራ መከፋፈል አለብን” ሲል ትዕዛዝ “ወ” ምክር ቢጤ አስተላልፏል።
ትርጉም፤ በአስፋው አብርሃ –
አቶ ሰላሙ ሃይሌ አስፋው አብረሃ የተረጎመውን በማያያዝ ከላኩት መጠነኛ እርማት ተደርጎ በነጻ አስተያየት የተለጠፈ፤