ብሮድካስት ባለስልጣን ሉዓላዊነት እና አብሮነትን በሚፈታተኑ ሚዲያዎች ላይ እርምጃ እንደሚወስድ አስታወቀ

የኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለስልጣን ሉዓላዊነት እና አብሮነትን የሚፈታተኑ ሚዲያዎች ላይ እርምጃ እንደሚወስድ አስታወቀ።

የባለስልጣኑ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ወንድወሰን አንዷለም ÷በትግራይ ክልል የተካሄደውን የህግ ማስከበር ዘመቻ ተከትሎ በትግራይ ክልል የተፈጠሩ ክስተቶችን አንዳንድ የውጭ መገናኛ ብዙኃን በአድልዎ የተሞላ፣ ሚዛናዊ ያልሆነ፣ የትክክለኛነት ችግር ያለበት፣ በተለያዩ ፍላጎቶች የተተበተበ እና የተለየ ተልዕኮ ያነገቡ ዜናዎችን፣ ዘጋቢ ፊልሞችን እና ሌሎች ዘገባዎችን እየሰሩ እንደሆነ የሚዲያ ሞኒተሪንግ የሁኔታ ግምገማ ያመላክታል ብለዋል።

አንዳንድ ዓለም አቀፍ ሚዲያ ተቋማት የሰሯቸው ዘገባዎች በአጠቃላይ የጋዜጠኝነት ሙያ አስተምህሮቶች እና ሙያዊ የስነ ምግባር ጥያቄዎችን የሚያስነሳ ነው ያሉት አቶ ወንድወሰን ÷ ሥራዎቻቸው በጣም የሚያስተዛዝቡና የሚያበሳጩ ጭምር መሆናቸውን አመልክተዋል።

የተፋለሰ፣ የተዛባና ከራሱ ጭምር የተጣላ የዜና አዘጋገብ የተከተሉበት የተለያዩ ምክንያቶች ሊኖሩ እንደሚችሉ የጠቆሙት ምክትል ዳይሬክተሩ÷ የተፋለሱ እና የተዛቡ ዘገባዎችን የሚሰሩ አንዳንድ ጋዜጠኞች በጥቅም የሚዘወሩ ናቸው ብለዋል።

የተዛቡ ዘገባዎችን ሲያስተላልፉ የነበሩ አንዳንድ ጋዜጠኞች ከዚህ ቀደም በሀገሪቱ ስልጣን ላይ ከነበረው እና ህግ የማስከበር እርምጃ ከተወሰደበት ቡድን መሪዎች እና አጀንዳ አዘጋጆች ጋር ወዳጅነት ያላቸው መሆናቸውን በተጨባጭ ማስረጃ ማረጋገጥ መቻሉንም ነው የተናገሩት ።

ዓለም አቀፍ ሚዲያ እና ዘገባዎችን የሚሰሩ ባለሙያዎችን ለይቶ ማየት ያስፈልጋል የሚሉት አቶ ወንድወሰን ÷ አንድ የሚዲያ ተቋም የላከው ጋዜጠኛ ስህተት ሰራ ማለት ሚዲያዎቹ ሙሉ በሙሉ ከእውነት፣ ከፍትህ እና ከሀቅ የተፋቱ ናቸው የሚል ድምዳሜ ላይ መድረስ እንደማያስችል አንስተዋል።

የተዛቡ ዘገባዎችን እንዲሰሩ እያደረጋቸው ያለው የመረጃ እጥረት ይሆን የሚል ጥያቄ የቀረበላቸው ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ የመረጃ ቅብብል እና እየሆነ ያለውን ነገር በትክክል ከማስተላለፍ አንጻር ችግሩ እንደ ሀገር ያለ ችግር መሆኑን ባይክዱም፤ የውጭ ሚዲያዎች የትግራይን ሁኔታ በተሳከረ መንገድ እንዲዘግቡ ያደረጋቸው የመረጃ እጥረት ነው ብለው እንደማያምኑ ገልጸዋል።

እንደ ሀላፊው ማብራሪያ ሚዲያዎች በትግራይ ክልል ገብተው ለመዘገብ ጥያቄ ማቅረባቸውን ተከትሎ በስፍራው ሄደው እንዲዘግቡ መንግሥት ፈቅዷል።

መንግሥት ከፈቀደ በኋላ ወደ ክልሉ የገቡ ጋዜጠኞች ሚዛናዊነት የጎደለው፣ በአድልኦ የተሞላ፣ የትክክለኛነት ችግር ያለበት፣ ለአንድ አካል የወገነ እንዲሁም የኢትዮጵያ መንግሥትና ህዝብ ክልሉን መልሶ ለመገንባት እያደረጉ ያለውን ጥረት ሙሉ በሙሉ የካደ ዘገባ እየሰሩ መሆኑን ጠቅሰው ይህም የመረጃ እጥረት እንዳልሆነያመላክታል ነው ያሉት።

See also  ትህነግ - በሰሜን ወሎና በጎንደር የህዝቡን የኢኮኖሚ መሰረቶች በሙሉ ማውደሙና መዝረፉ ይፋ ሆነ

እንደ አቶ ወንድወሰን ማብራሪያ ፣የመገናኛ ብዙሃን ባለሥልጣን ከዚህ ቀደም የተዛቡ ዜናዎች እና ዜና ነክ ዘገባዎችን ሲያሰራጩ የነበሩ ጋዜጠኞች ላይ የሥራ ፍቃድ እስከመሰረዝ የደረሰ እርምጃ ወስዷል።

አንዳንድ ወኪሎችን ከሀገር አስወጥቷል ፣በአንዳንዶች ላይ ጥብቅ ማስጠንቀቂያ ፅፎባቸዋል።

የተዛቡ ዘገባዎችን በሚሰሩ ባለሙያዎች ላይ የተወሰዱ እርምጃዎች የመጨረሻ ግብ አይደሉም ያሉት አቶ ወንድወሰን፤ በቀጣይም የሀገሪቱን ሉዓላዊነት የሚዳፈሩ፣ አብሮነትን የሚፈታተኑ ሥራዎችን የሚሰሩ ሚዲያዎችና ባለሙያዎች ላይ እርምጃዎችን እንደሚወስድ መናገራቸውን ኢፕድ ዘግቧል።

  • የተጠልፈቸው ጸጋ በላቸው ነጻ ሆነች፤ ጠላፊው አልተያዘም
    ወይዘሪት ፀጋ በላቸውን ከተጠርጣሪው ግለሰብ ማስጣል መቻሉን የሲዳማ ክልል ሰላምና ጸጥታ ቢሮ አስታወቀ። የሲዳማ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ሃላፊ አቶ አለማየሁ ጢሞቲዮስ ጉዳዩን አስመልክተው በሰጡት መግለጫ በተደረገው የተቀናጀ የፀጥታ ኦፕሬሽን በተጠርጣሪው ግለሰብ የተጠለፈችውን ወይዘሪት ፀጋ በላቸውን ማስጣል መቻሉን ተናግረዋል። ግንቦት 15 ቀን 2015 ከመደበኛ ስራዋ ወጥታ ወደቤቷ ስታቀና ተጠርጣሪው ግለሰብContinue Reading
  • ፌደራል ፖሊስ ሆን ብለው ሐሰተኛ መረጃ በሚያሰራጩ አካላት ላይ እየተወሰደ ያለው እርምጃ ተጠናክሮ ይቀጥላል አለ
    ሆን ብለው ሕብረተሰቡን ለማሳሳት ሐሰተኛ መረጃ በሚያሰራጩ ግለሰቦች ላይ እየወሰደ ያለውን እርምጃ አጠናክሮ እንደሚቀጥል የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ አስታወቀ። ተቋሙ አገራዊ ለውጡን ተከትሎ መንግስት ለህዝብ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት ከወሰዳቸው እርምጃዎች መካከል የሰብአዊ መብት ጥሰት ይፈፀምበት የነበረውን ማዕከላዊ የወንጀል ምርመራን መዝጋት መሆኑንና ይሄንን ተከትሎ በፖሊስ የወንጀል ምርመራ ስራ ላይ ግልጽነትና ተጠያቂነት የሰፈነበትContinue Reading
  • ኢሰመኮ ሁለት ሰዎች ሲሞቱ በርካቶች የጸጥታ ሃይሎችን ጨምሮ ጉዳት እንደደረሰባቸው አስታወቀ
    በሸገር ከተማ ከመስጊዶች መፍረስ ጋር ተያይዞ የተነሱ ተቃውሞዎችን እና የደረሰ ጉዳትን በተመለከተ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ከግንቦት 18 ቀን 2015 ዓ.ም. ጀምሮ በተለይም በአዲስ አበባ አንዋር መስጊድ ውስጥ እና በተወሰኑ አካባቢዎች በሸገር ከተማ በመንግሥት አካላት ከፈረሱ መስጊዶች ጉዳይ ጋር ተያይዞ የተነሱ ተቃውሞዎችን ተከትሎ የደረሰውን የሰዎች ሞት እና ጉዳቶችን በተመለከተContinue Reading
  • አዲስ አበባና በሸገር ከተሞች የፈረሱትን ቤቶችና ማህበራዊ ቀውስ አስመልክቶ ኢሰመኮ መገለጫ አወጣ
    በአዲስ አበባ እና በኦሮሚያ ክልል ሸገር ከተሞች እየተካሄደ ነው ባለው የቤት ፈረሳ እና የግዳጅ የማስነሳት ሂደት 111 ሺህ 811 ቤቶች መፍረሳቸውን የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ጉባዔ (ኢሰመጉ) አስታወቀ። ኢሰመጉ ይህንን የገለጸው ከጥቅምት 2015 ዓ.ም. ጀምሮ በጉዳዩ ላይ ያካሄደውን የምርመራ ሪፖርት ግንቦት 23/2015 ዓ.ም. ይፋ ባደረገበት ጊዜ ነው። ኮሚሽኑ ይህንን አሃዝ ይፋContinue Reading

Leave a Reply