10 ሚሊየን ብር የሚገመት ጥፍጥፍ ወርቅ ከግል ተበዳይ አስፈራርተው ወስደዋል የተባሉ ግለሰቦች በከባድ የሙስና ወንጀል ተከሰሱ፡፡ ክሱ የቀረበው በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ተረኛ ችሎት ሲሆን÷ችሎቱ ዛሬ ከሰዓት በኃላ የክሱን ዝርዝር በንባብ አሰምቷል።
ተከሳሾቹ 1ኛ ተከሳሽ የቀድሞ የአዲስ አበባ ከተማ የሰላም እና ፀጥታ ዘርፍ አባልና የቀድሞ ወታደር የነበረው ሻለቃ ፀጋዬ ሃይሉ፣ 2ኛ ደበበ ገመዳ፣ 3ኛ ሰናይት ብርሃኑ፣ 4ኛ አለማየሁ ደነቀ እና 5ኛ አሚር ወርቁ ናቸው።
የፍትሕ ሚኒስቴር የሙስና ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ዐቃቤ ሕግ በተከሳሾቹ ላይ ሁለት የሙስና ወንጀል ክሶችን አቅርቦባቸዋል።
ተከሳሾቹ የወንጀል ህግ አንቀጽ 32 ንዑስ ቁጥር 1 ሀ/ለ እና አንቀጽ 33 እንዲሁም የሙስና ወንጀሎችን ለመደንገግ የወጣውን አዋጅ ቁጥር 881/2007 አንቀጽ 9 ንዑስ ቁጥር 1ሀ /ሐ እና ንዑስ ቁጥር 2 ስር የተደነገገውን ድንጋጌ በመተላለፍ እና በወንጀል የተገኘ ንብረትን ወይም ገንዘብን ሕጋዊ አስመስሎ ማቅረብ የወንጀል ክስ ነው የተመሰረተባቸው።
በክሱ ላይ እንደተመላከተው÷ የካቲት 21 ቀን 2015 ዓ.ም የግል ተበዳይ ከትግራይ ክልል ይዞት የመጣውን 1 ሺህ 611 ግራም ጥፍጥፍ ወርቅ ለማሰራት ወደ ፒያሳ ከ3ኛ ተከሳሽ ጋር አብረው ሲጓዙ 3ኛ ተከሳሽ 1ኛ፣2ኛና 4ኛ ተከሳሾች የመንግስት የፀጥታ አካላት መስለው ወርቁን እንዲወስዱበት ለማድረግ በመስማማትና ተከሳሾቹ ወደ ሚገኙበት ቃተኛ ተብሎ ወደሚጠራ ምግብ ቤት ምሳ እንብላ በማለት የግል ተበዳይን ወደ ምግብ ቤቱ ወስዳለች፡፡
ምግብ ቤት እንደደረሱ 1ኛ ተከሳሽ የወታደር ልብስ በመልበስ እራሱን ወታደርና የፀጥታ አካል አስመስሎ የግል ተበዳይ ወደነበረበት ተሽከርካሪ በመቅረብ ተበዳይ ተቀምጦበት ወደነበረው የሹፌር ወንበር እንዲወርድና ከኋላ እንዲቀመጥ ካደረገው በኋላ እራሱ ተከሳሹ ወደመኪናው ገብቶ ጋቢና ከተቀመጠ በኋላ መኪናው በሕገወጥ መንገድ ሀገር ውስጥ የገባና ነው በማለትና መኪናውን በጂፒኤስ እየተከታተሉት መሆኑን በመግለጽ መኪናው ይታሰራል ሲል እንዳስፈራራ በክሱ ተጠቅሷል።
ሁለተኛ ተከሳሽ ደግሞ የመኪናው የኋላ ወንበር ላይ ገብቶ በመቀመጥና ሽጉጥ አውጥቶ የግል ተበዳይ ጭንቅላት ላይ በመደቀን የግል ተበዳዩ ይዞት የነበረውን የዋጋ ግምቱ 10 ሚሊየን ብር የሆነ 1ሺህ 611 ግራም ጥፍጥፍ ወርቅ ነጥቆ መውሰዱ በክሱ ተመላክቷል።
ወርቁን ከነጠቁት በኃላ ተበዳዩን ከመኪናው በማስወረድ በ3ኛ አሽከርካሪነት ጥፍጥፍ ወርቁን ይዘው በርቀት ሆኖ ሲጠብቃቸው ከነበረ 4ኛ ተከሳሽ ጋር በመሆን ወርቁን ፒያሳ አካባቢ በመውሰድ ሕጋዊ ንግድ ፍቃድ ለሌለው ለ5ኛ ተከሳሽ በ3 ሚሊየን 415 ሺህ በመሸጥ እና ገንዘቡን በተለያየ መጠን በመከፋፈል ለግል ጥቅም አውለዋል በማለት ዐቃቤ ሕግ የተከሳሽን ሚና ዘርዝሮ ስልጣንን ያለአግባብ መጠቀም ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ አቅርቧል።
ከ1ኛ እስከ 4ኛ ተራ ቁጥር የተጠቀሱ ተከሳሾች በተረኛ ችሎት ቀርበው ክሱ ከደረሳቸው በኋላ የክስ ዝርዝሩ በችሎት በንባብ ተሰምቷል።
የተከሳሽ ጠበቆች ክሱ በችሎት ከተነበበ በኃላ ዋስትና ላይ ክርክር ለማድረግና የክስ መቃወሚያ ለማቅረብ አጭር ቀጠሮ እንዲሰጣቸው ተረኛ ችሎቱን ጠይቀዋል።
ዐቃቤ ህግ በኩል በጠበቆች የቀጠሮ ጥያቄ መቃወሚያን በሚመለከት አልቃወምም በማለት አስተያየት ሰጥቷል።
ይሁንና ተረኛ ችሎቱ ግን የተከሰሱበት አንቀጽ ዋስትና እንደሚያስነፍግ በማብራራት ተከሳሾቹ የክስ መቃወሚያ እስኪያቀርቡ ድረስ ባሉበት ማረፊያ ቤት እንዲቆዩ ትዕዛዝ ተሰጥቷል።
የተከሳሾች የክስ መቃወሚያ ካላቸው ለመጠባበቅ ለነሐሴ 11 ቀን 2015 ዓ.ም ቀጠሮ ተሰጥቷል።
በታሪክ አዱኛ ፋና
- የበርሊን ማራቶን ባለማዕረግ ትግስት እነ ዱቤ ጂሎ ቢሳተፉ ታዝረከርካቸው ነበርበማራቶን ከሁለት ደቂቃ በላይ ማሻሻል እጅግ የሚደነቅና ያልተለመደ ነው። ባለሙያዎቹ ወይም አሰልጣኞቹ የሮጠችበትን ፍጥነት በሰዓትና ርቀት ከፋፍለው ቢያቀርቡት ምን አልባትም ወንዶችን የሚገዳደር ፍጥነት ተጠቅማ ሮጣለች። የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ተቴክኒክ ዳይሬክተርና የአትሌቶች ኮሚሽን ሰብሳቢ የነበሩት የዛሬው የተከበሩ ዱቤ ጅሎ አይነቱን ሯጮችን አዝረክርኮ ማሸነፍ የሚያስችላትን ሃይል አሳይታለች። የበርሊና ባለ ማዕረግ ትዕግስት!! ተግስት … Read moreContinue Reading
- ለወልቃይት ጠገዴ ሴቲት ሁመራ አንድ ሚሊዮን የጉልበት ሰራተኛ ይፈለጋል፤ ከአንድ ነጥን አንድ ሚሊዮን ኩንታል በላይ ሰሊጥ ይጠበቃል“ከየትኛውም የኢትዮጵያ ክልል አስተማማኝ ሰላም ያለው እዚህ ነው። ለሰራተኞች እንደ ቤተሰብ ዝግጅት አድርገናል። ኑ” ሲሉ የተሰሙት አምስት መቶና ሶስት መቶ ሄክታር ሰሊጥና ማሽላ ያመረቱ ባለሃብቶች ናቸው። የዞኑ ግብርና ቢሮ ሃላፊ እንዳሉት አንድ ሚሊዮን አንድ መቶ ሃምሳ ሁለት ሺህ ኩንታል የሰሊጥ ምርት ስለሚጠበቅ ከአንድ ሚሊዮን በላይ የሰራተኛ ሃይል ያስፈልጋል። የዞኑ አርባ … Read moreContinue Reading
- የጎንደርን ከተማ ምን አይነት ተኩስ እንደሌለ ተገለጸ፤ ጎንደር ተይዛለች ተብሎ ነበር“ጎንደር ከተማን ሙሉ በሙሉ ይዘናታል” ሲሉ ስማቸው እንዳይገለጽ ጠይቀው ለጀርመን ድምጽ መረጃ በሰጡ የአማራ ሕዝባዊ ኃይል ፋኖ ቃል አቀባይ አየር ማረፊያውን ሆን ብለው እንዳልያዙ አመልክተዋል። እሳቸው ተናገሩ የተባለው በጀርመን ድምጽ እየተሰማ በለበት ሰዓት በተመሳሳይ የጎንደር ከተማ አስተዳደር ውጊያ መደረጉን ሳያስተባብል ከተማዋን ለመያዝ የገባው ሃይል መደምሰሱን አሃዝ ጠቅሶ አመልክቷል። አገር መከላከያም … Read moreContinue Reading
- “የሞተው ባልሽ ገዳዩ ወንድምሽ፣ሀዘንሽ ቅጥ አጣ ከቤትሽ አልወጣ”የሞተው ባልሽ ገዳዩ ወንድምሽ (ሀዘንሽ ቅጥ አጣ ከቤትሽ አልወጣ) የሚለው የቆየ ተረት ልብን የሚያደማ ኩነትን ማሳያ ነው። እቺ መከረኛ ሚስት ባልዋ በእናቷ ልጅ ወንድሟ ተገደለ። ሟች ባል፣ ገዳይ ወንድም … ኢህአፓ “ሃይማኖት ነው” በሚል ሲገልጸው በነበረው ትግል በቀይና ነጭ ሽብር ስም እናቶች የወላድ መካን ሆነዋል። ጧሪ ያጡና ባዶ ቤት ሃዘን … Read moreContinue Reading
- በአማራ ክልል የተነሳው ጦርነት በሰላም ሊቆጭ እንደሚችል ተሰማበአማራ ክልል የተቀሰቀሰው ጦርነት በሰላማዊ መንገድ የሚቋጭበት አግባብ ተስፋ ሰጪ ደረጃ መድረሱ ተሰማ። የኢትዮ12 የዜና አቀባዮች እንዳሉት ሰላም ወደድ የሆኑ ዜጎች ችግሩን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት እያደረጉ ያለው ጥረት ውጤታም እየሆነ መሆኑንን ነው ያመለከቱት። በሰላም ጥረቱ ውስጥ የሚሳተፉትን ወገኖችና የሰላም ንግግር አመቻች የሆኑትን ክፍሎች ሳይጠቅሱ የዜናው ሰዎች እንዳሉት ጥረቱ ብዙ መንገድ … Read moreContinue Reading