ከተማ አስተዳደሩ ዛሬ ባወጣው መግለጫ ÷የከተማ አስተዳደሩ እና የከተማዋ ነዋሪዎች እንደ ከዚህ ቀደሙ ሁሉ ዛሬም ከክልሉ መንግስት እና ሕዝብ ጎን በመቆም ይሄንን ሀገር አፍራሽ እና የዘራፊ ስብስብ ኢሰብአዊ ድርጊቱን በፅኑ ይቃወማል! ብሏል፡፡
ከመከላከያ ሰራዊት ጎን በመቆም እንደ ወትሮው ሁሉ ደጀንነቱን ያረጋግጣል! የከተማውን ሰላም በማረጋገጥ የህገ-ወጦችን ተግባር በህግ ሥርአት ያስከብራል! ሲልም ገልጿል።
ክልል ከጦርነት ጉዳት ሳያገግም በስሙ ምለው በሚገዘቱ የጥፋት ኃይሎች ይህን አይነት አስከፊ ችግር ስላጋጠመው እያዘነ ፤ እንደ አስፈላጊነቱ የከተማ አስተዳደሩ በሁሉም ረገድ ከክልሉ ህዝብና መንግስት ጎን በመቆም ይህንን አጥፊ ቡድን ኢሰብአዊ ድርጊቶቹን እንደሚቃወምም አስታውቋል።
የዚህ የጥፋት ኃይል ከአማራ ክልል ቀጥሎ አዲስ አበባን የሽብር እና የብጥብጥ ማዕከል ለማድረግ በተለያየ መንገድ እየሞከረ እንደሚገኝም ተደርሶበታል ነው ያለው በመግለጫው።
እነዚህ አጥፊ ቡድኖች እራሳቸው በጠመቁት የፀብ አጀንዳ አዲስ አበባን እና የአዲስ አበባን ህዝብ የአላማቸው ማስፈፀሚያ ለማድረግ ከተማዋን ደግሞ የግጭት እና ብጥብጥ አውድ ለማድረግ በተግባር እየተንቀሳቀሱ እንደሚገኙም ገልጿል፡፡
ሆኖም ሰላም ወዳዱ እና ሚዛናዊው የአዲስ አበባ ከተማ ህዝብ ግዜውን፣ እውቀቱን፣ ገንዘቡን እና ጉልበቱን ለሰላም እና ልማት የሚያውል ቢሆንም፣ በህልውናው ላይ በሰላሙ ላይ እና በልማቱ ላይ የሚቃጣን ማንኛውንም አደጋ እና ስጋት እንደ ወትሮው ሁሉ በግንባር ቀደምነት ይፋለማል። ልማቱንም ያስቀጥላል !! ብሏል የከተማ አስተዳደሩ በመግለጫው፡፡
ይህ የጥፋት ቡድን ለዚህ እኩይ ዓላማው ማስፈፀሚያነት የሚያገለግሉና ምንም አይነት ግጭት ከሌለበት አካባቢ የግጭት ሽሽት እና ተፈናቃይ በማስመሰል በርካታ ፀጉረ-ልውጦችን አስርገው በማስገባት በከተማው ውስጥ የጥላቻ፣ የመከፋፈል እና የአመፅ አላማቸውን ለማራመድ እና የጠመቁትን ሴራ ወደ ህዝቡ ለመርጨት ሲሞክሩ በእኩይ ተግባራቸው ሲንቀሳቀሱ መያዛቸውንም ገልጿል፡፡
ከተማ አስተዳደሩ እንደ ሁል ጊዜው ሁሉ በቁርጠኝነት ህገ ወጦችን በህግ ስርዓት ያስይዛል!ሲልም በመግለጫው አስፍሯል፡፡
በመሆኑም የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ይህንን መሰል እንቅስቃሴ በንቃት እየተከታተለ ለህዝቡ ይፋ የሚያደርግ ሲሆን ህዝቡን ያሳተፈ እርምጃዎችንም እንደሚወስድም አስታውቋል፡፡
በተጨማሪም እንደ አገር የገጠመን ይህንን ችግር የጋራ ርብርብ የሚሻ በመሆኑ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እና የከተማችን ነዋሪዎች ከጀግናዉ የመከላከያ ስራዊታችን፤ ከአማራ ክልል መንግስት እና ህዝብ ጎን በመቆም እንደ ወትሮው ሁሉ አስፈላጊውን ቁርጠኛ ድጋፍ ያደርጋል!! ብሏል፡፡
ሰላም ወዳድነቱን በሥራ እና ደጀንነቱን በቁርጠኛ ትግል ያረጋግጣል! ሲል ገልጿል በመግለጫው፡፡
…………………………………………………………………..
- ምን ያክል ተዘጋጅተናል? ጥድፊያ አገር አልባ ለመሆን !! ህጻናቱ ምን አጠፉ?ያለፈውን ግማሽ ምዕተ ዓመት የኢትዮጵያ ፖለቲካ እና ሥነ መንግሥት ታሪክ በጥሞና የተከታተለ ኢትዮጵያዊ የግዛት አንድነቷን እና የፖለቲካ ነጻነቷን በአንጻሩ… Read more: ምን ያክል ተዘጋጅተናል? ጥድፊያ አገር አልባ ለመሆን !! ህጻናቱ ምን አጠፉ?
- የትግራይ ክልል ታጣቂዎች ዳግም ዝርፊያ እያፈጸሙ ነው፤ የተማሪዎች መጽሃፍትን “የአማራ ክልል ናቸው እየሉ ቀደዋል”በአላማጣ ከተማ በተለየ መልኩ የትግራይ ክልል ታጣቂዎች በከተማዋ ውስጥ እንደሚንቀሳቀሱ ነዋሪዎች መመስከራቸውን ቢቢሲ አስታወቀ። ይህ የተገለጸው ከአለማጣ እና አካባቢው… Read more: የትግራይ ክልል ታጣቂዎች ዳግም ዝርፊያ እያፈጸሙ ነው፤ የተማሪዎች መጽሃፍትን “የአማራ ክልል ናቸው እየሉ ቀደዋል”
- በዘንድሮው ዓመት የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ኢትዮጵያ ሰባት ነጥብ ሁለት ቢሊዮን ችግኝ ልትተክል ነውለዘንድሮ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር 6 ነጥብ 5 ቢሊየን ችግኝ ለመትከል ዕቅድ መያዙንna ለዚህም ተግባራዊነት ከሰባት ነጥብ ሁለት ቢሊየን በላይ… Read more: በዘንድሮው ዓመት የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ኢትዮጵያ ሰባት ነጥብ ሁለት ቢሊዮን ችግኝ ልትተክል ነው
- አፍሪካ ህብረት ” የውጭ ምንዛሪ ሒሳቡን ወደ ሌላ ሀገር ሊያዘዋውር ነው” የሚለው ዜና ሃሰት መሆኑን አረጋገጠአፍሪካ ህብረት የውጭ ምንዛሬ አካውንቱን ወደ ሌላ አገር እንደሚያዘዋውር ተጠቅሶ በህብረቱ ስም የወጣው ዜና ሃሰት፣ ሆን ተብሎ የተቀነባበረ መሆኑን… Read more: አፍሪካ ህብረት ” የውጭ ምንዛሪ ሒሳቡን ወደ ሌላ ሀገር ሊያዘዋውር ነው” የሚለው ዜና ሃሰት መሆኑን አረጋገጠ
- አፍሪቃ ህብረት ምን አሰጋውና “ገንዘቤን ወደ ሌላ አገር ለማዛወር እያሰብኩ ነው” ሲል ተንሿከከ፤ የጾምና የፍስክ ዜናዎችባንኩ የክፍያ ሰነድ ቀረበለት። ማጣሪያ ጥያቄ ለህብረቱ አቀረበ። ሃሰት ሆኖ ተገኘና ፖሊስ ተጠርጣሪዎቹን ያዘ። ጉዳዩ ወደ ህግ አመራ። አሁን… Read more: አፍሪቃ ህብረት ምን አሰጋውና “ገንዘቤን ወደ ሌላ አገር ለማዛወር እያሰብኩ ነው” ሲል ተንሿከከ፤ የጾምና የፍስክ ዜናዎች