- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለአማራ ክልል መንግስትና ህዝብ ያለውን አጋርነት ገለጸ፡፡
ከተማ አስተዳደሩ ዛሬ ባወጣው መግለጫ ÷የከተማ አስተዳደሩ እና የከተማዋ ነዋሪዎች እንደ ከዚህ ቀደሙ ሁሉ ዛሬም ከክልሉ መንግስት እና ሕዝብ ጎን በመቆም ይሄንን ሀገር አፍራሽ እና የዘራፊ ስብስብ ኢሰብአዊ ድርጊቱን በፅኑ ይቃወማል! ብሏል፡፡
ከመከላከያ ሰራዊት ጎን በመቆም እንደ ወትሮው ሁሉ ደጀንነቱን ያረጋግጣል! የከተማውን ሰላም በማረጋገጥ የህገ-ወጦችን ተግባር በህግ ሥርአት ያስከብራል! ሲልም ገልጿል።
ክልል ከጦርነት ጉዳት ሳያገግም በስሙ ምለው በሚገዘቱ የጥፋት ኃይሎች ይህን አይነት አስከፊ ችግር ስላጋጠመው እያዘነ ፤ እንደ አስፈላጊነቱ የከተማ አስተዳደሩ በሁሉም ረገድ ከክልሉ ህዝብና መንግስት ጎን በመቆም ይህንን አጥፊ ቡድን ኢሰብአዊ ድርጊቶቹን እንደሚቃወምም አስታውቋል።
የዚህ የጥፋት ኃይል ከአማራ ክልል ቀጥሎ አዲስ አበባን የሽብር እና የብጥብጥ ማዕከል ለማድረግ በተለያየ መንገድ እየሞከረ እንደሚገኝም ተደርሶበታል ነው ያለው በመግለጫው።
እነዚህ አጥፊ ቡድኖች እራሳቸው በጠመቁት የፀብ አጀንዳ አዲስ አበባን እና የአዲስ አበባን ህዝብ የአላማቸው ማስፈፀሚያ ለማድረግ ከተማዋን ደግሞ የግጭት እና ብጥብጥ አውድ ለማድረግ በተግባር እየተንቀሳቀሱ እንደሚገኙም ገልጿል፡፡
ሆኖም ሰላም ወዳዱ እና ሚዛናዊው የአዲስ አበባ ከተማ ህዝብ ግዜውን፣ እውቀቱን፣ ገንዘቡን እና ጉልበቱን ለሰላም እና ልማት የሚያውል ቢሆንም፣ በህልውናው ላይ በሰላሙ ላይ እና በልማቱ ላይ የሚቃጣን ማንኛውንም አደጋ እና ስጋት እንደ ወትሮው ሁሉ በግንባር ቀደምነት ይፋለማል። ልማቱንም ያስቀጥላል !! ብሏል የከተማ አስተዳደሩ በመግለጫው፡፡
ይህ የጥፋት ቡድን ለዚህ እኩይ ዓላማው ማስፈፀሚያነት የሚያገለግሉና ምንም አይነት ግጭት ከሌለበት አካባቢ የግጭት ሽሽት እና ተፈናቃይ በማስመሰል በርካታ ፀጉረ-ልውጦችን አስርገው በማስገባት በከተማው ውስጥ የጥላቻ፣ የመከፋፈል እና የአመፅ አላማቸውን ለማራመድ እና የጠመቁትን ሴራ ወደ ህዝቡ ለመርጨት ሲሞክሩ በእኩይ ተግባራቸው ሲንቀሳቀሱ መያዛቸውንም ገልጿል፡፡
ከተማ አስተዳደሩ እንደ ሁል ጊዜው ሁሉ በቁርጠኝነት ህገ ወጦችን በህግ ስርዓት ያስይዛል!ሲልም በመግለጫው አስፍሯል፡፡
በመሆኑም የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ይህንን መሰል እንቅስቃሴ በንቃት እየተከታተለ ለህዝቡ ይፋ የሚያደርግ ሲሆን ህዝቡን ያሳተፈ እርምጃዎችንም እንደሚወስድም አስታውቋል፡፡
በተጨማሪም እንደ አገር የገጠመን ይህንን ችግር የጋራ ርብርብ የሚሻ በመሆኑ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እና የከተማችን ነዋሪዎች ከጀግናዉ የመከላከያ ስራዊታችን፤ ከአማራ ክልል መንግስት እና ህዝብ ጎን በመቆም እንደ ወትሮው ሁሉ አስፈላጊውን ቁርጠኛ ድጋፍ ያደርጋል!! ብሏል፡፡
ሰላም ወዳድነቱን በሥራ እና ደጀንነቱን በቁርጠኛ ትግል ያረጋግጣል! ሲል ገልጿል በመግለጫው፡፡
…………………………………………………………………..
- ሸኔ መከፈሉ ተሰማ፤ በሺዎች የሚቆጠሩ ታጣቂዎቹ እጅ እየሰጡ ነው፤ ተማራኪዎቹ ድርጅቱ መፈረካከሱን አስታወቀ“የህግ የበላይነት ለማስከበር እየተወሰደ ያለዉን እርምጃ መቋቋም የተሳናቸው በሺዎች የሚቆጠሩ የአሸባሪዉ ሸኔ አባላት ለመንግስት እጅ ሰጡ” ሲል የዘገቡት መገናኛዎች እንዳሉት ድርጅቱ ቁመናው ፈርሷል። በቅርቡ በታንዛንያ ለስምምነት ብዙ ርቀት ከተኬደና ከንግገሩ መልካም ዜና የተጠበቀ ባለበት ወቅት ስምምነት ላይ እንዳልተደረሰ መንግስት ይፋ ማድረጉ ይታወሳል። በሰላም ንግግሩ የተኩስ ማቆም ስምምነት ተደርሶ እንደነበር፣ አነጋጋሪ … Read moreContinue Reading
- ሰው ሰራሽ ቦይ በመገንባት ቀይ ባህርን መቀላቀል የኢትዮጵያ ሌላ አማራጭ?አርተፊሻል ቦይ በመገንባት ቀይ ባህርን ወደ ኢትዮጵያ በማምጣት ኢትዮጵያ የባህር በር ሊኖራት ይችላል፤ ይህ በአለም ላይ በኢትዮጵያ የአፋር ምድር ረባዳነት የተነሳ ተፈጥሮ የሰጠው እድል ነው! በኢትዮጵያ እና በኤርትራ መካከል አርተፊሻል ቦይ በመስራት ኢትዮጵያ የወደብ ባለቤት መሆን ትችላለች፡፡ እንደዚህ አይነት አጋጣሚ ሊፈጠር የቻለው፤ የኢትዮጵያ የአፋር ቦታ ከባህር ወለል በታች እስከ 110 … Read moreContinue Reading
- ብሄራዊ ባንክ የገንዘብ ቁጥጥሩን አጠንክሮ እንደሚገፋበት አስታወቀ፤ ህገወጥ የወርቅ አዘዋዋሪዎች ላይ እርምጃ እየተወሰደ ነው– የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ አዲስ የማቋቋሚያ ረቂቅ አዋጅ አዘጋጀ በአገሪቱ የሚታየውን የዋጋ አለመረጋጋት ለመግራት የግንዘብ ስርጭት ላይ ጥብቅ ቁጥጥር በማድረግ የተጀመረው ስራ ውጤት እያሳየ መሆኑ ተመለከተ፤ ተጠናክሮ ክምሩ እንደሚሰራበትና ግሽበትን በዓመቱ መጨረሻ 20 ከመቶ ለማድረስ መታቀዱ ተሰማ። ህገወጥ የወርቅ ነጋዴዎች ላይ ጥብቅ ቁጥጥርና የማበረታቻ መደረጉ ለውጥ ቢያሳይም በቂ እንዳልሆነ ተመለከተ። … Read moreContinue Reading
- መንግስት የነዳጅ ድጎማን በህገወጥ መንገድ ሲጠቀሙ ነበሩ ያላቸውን 40 ሺህ ተሽከርካሪዎች ከስርአቱ አስወጣ፣ የሰርቁትን ይከፍላሉየታለመለት የነዳጅ ድጎማን ላልተገባ ዓላማ ሲጠቀሙ የነበሩ 40 ሺህ ተሽከርካሪዎች ከድጎማ ስርዓቱ እንዲወጡና ዕዳ እንዲከፍሉ መደረጉን የፕላንና ልማት ሚኒስትር ዶክተር ፍጹም አሰፋ ገለጹ። ሚኒስትሯ ይህን ያሉት የመንግሥት የ2016 የመጀመሪያ የሩብ ዓመት አፈጻጸም በተገመገመበት ወቅት ነው። የግምገማው ተሳታፊዎች መንግሥት የነዳጅ ድጎማን ጨምሮ በርካታ የህዝብ ተጠቃሚነትን የሚያረጋገጡ ተግባራትን ማከናወኑን አድንቀው፤ ሆኖም” ድጎማው … Read moreContinue Reading
- በዓመት አምስት ሚሊዮን ቶን ሲሚንቶ የሚያመርተው ፋብሪካ ከመጋቢት በሁዋላ የሲሚንቶ ዋጋ ወደ ነበረበት የሚመልሰ ነውበቀን 10 ሺህ ቶን ሲሚንቶ እንዲያመርት እቅድ ተይዞለት በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን እንሳሮ ወረዳ ለሚ ከተማ እየተገነባ ያለውን የለሚ ናሽናል ሲሚንቶ ፋብሪካ የግንባታ በመጋቢት ወር ይጠናቀቃል። ምርቱ በተባለው ወር ሲጀምር የሲሚንቶ ዋጋ አሁን ካለበት በግማሽ እንደሚወርድ ይጠበቃል። ከመጋቢት በሁዋላ ፋብሪካው በ50 በመቶ የሲሚንቶ እጥረቱን ያስወግዳል። ኢስት አፍሪካን ሆልዲንግ ኩባንያ … Read moreContinue Reading