ለግማሽ መዕተ ዓመት ራሱን “የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር (ትሕነግ) ” በማለት የሚጠራው ድርጅት እጅግ አነጋጋሪ ግብረ ምላሽ ሰጠ። ለፌደራል መንግስት በሰጠው ምላሽ ” በትግራይም ሆነ በሌሎች የኢትዮጵያ አካባቢዎች ሰላም እንዲሰፍን በሚደረግ ተግባር ውስጥ ከመንግስት ጋር አልተባበርም” ነው ያለው።
ከሁለት ወራት ግምገማ በሁዋላ ሰፊ መግለጫ በትግርኛ ቋንቋ በማውጣት የፊደራል መንግስት የትግራይ ክልልን በፕሪቶሪያው ስምምነት መሰረት እንዳላስተናገደ ጠቅሶ ሰፊ ወቀሳ የሰነዘረው ትህነግ፣ ስምምነቱ ሙሉ በሙሉ ተጋራዊ እንዲደረግ ክልሉን የማቋቋምና መልሶ የመገንባት ስራውም ዝቅተኛ በመሆኑ ሊታሰብበት እንደሚገባ አስገንዝቦ ነበር።
የፊደራል መንግስት ከሰላሳ ሰባት ቢሊዮን ብር በላይ መስጠቱን ዘርዝሮ በጥር 23 ቀን 2016 ዓም ምላሽ ሲሰጥ የትግራይና የአማራ ክልል የይገባኛል ይዞታን አስመልክቶ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ በህዝበ ውሳኔ እንዲፈታ ስራ እየተሰራ መሆኑን ጠቁም የፕቲርቶሪያው ስምምነት ተግባራዊ እንዲሆን ቁርጠኛ አቋም እንዳለው አስታውቆ ነበር።
ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ትግራይ በተመለከተ ለቀረበላቸው ጥያቄ ምላሽ ሲሰጡ “ከድርድሩ ጋር በተያያዘ ለህዝብ ምንም የተደበቀ ነገር የለም” ሲሉ ተደምጠዋል። ምንም የተደበቀ ነገር እንደሌለ ጠቅሰው ከድርድሩ በኋላ በጋራ የተሰሩ ስራዎችን ከ37 ቢሊዮን ብር ድጋፍ ያልተካተቱ ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትሩ የሚከተሉትን ለማሳያ ገልጸዋል።
• በትግራይ ያሉትን አየር መንገዶች ለመጠገን ግማሽ ቢሊዮን ብር ወጪ ወጥቷ ፡፡
• በቴሌ መሰረተ ልማቶች ላይ በተሰራውስራ 20ሺህ ዜጎች የቤት ለቤት ስልክ ጥገና ተደርጎላቸዋል ብለዋል፡፡
• ከኤልክትሪክ መሰረተ ልማት ጋር በተያያዘም በሁሉም ከተሞች መብራት ጥገና እንደተደረገላቸው አብራርተዋል፡፡
• ትግራይ ውስጥ ያሉ ሁሉም ሃይስኩሎች ስራ እና ትምህርት መጀመራቸውንም አንስተዋል፡፡
• ዩኒቨርስቲዎችም ወደ መማር ማስተማር ስራቸው ተመልሰዋል ሲሉም ነው የተናገሩት፡፡
• ከ200 በላይ የሚሆኑ ኢንዱስትሪዎች ስራ ጀምረው ዜጎችን ተጠቃሚ እያደረጉ ናቸው ብለዋል፡፡
• ለትግራይ ክልል 500 ትራክተሮች ለአርሶአደሮች እንዲከፋፈሉ ግዢ ተፈሞ ጅቡቲ ደርሰዋል። ማረስና ችግርን በራስ ለመወጣት ተግቶ መስራት አማራጭ እንደሆነ አክለዋል። ይህን ቢሉም ጠቅላይ ሚኒስትሩ አቅም ቢፈቅድ ክልሉ ከዚህ በላይ ያስፈልገዋል ብለዋል።
ለዚህ የጠቅላይ ሚኒስትሩ መግለጫ የትግራይ ክልል ምን እንደሚመልስ ባይታውቀም ቀደም ሲል በዝርዝር ተተንትኖ 37 ቢሊዮን ብር በላይ ለትግራይ መድረሱ አስመልክቶ የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጽህፈት ቤት ለሰጠው ምላሽ ከትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ዘንድ ምንም የተሰጠ ምላሽ የለም። ይሁን እንጂ የወልቃይት ጠገዴን ጉዳይ ብቻ ነቅሶ በማውጣት ማስጠንቀቂያ መሰል ምላሽ ሰጥቷል።
መንግስት ከሰላሳ ቢሊዮን ብር በላይ ወደ ትግራይ ማስተላለፉን፣ ለምን ተግባርባ ለየትኛው ተቋም ድጋፍ ማድረጉን አስልቶ ያወጣው መግለጫ ” ብሩ የት ገባ?” የሚል መወያያ ማስነስነሳቱን ተከትሎ ከትግራይ አስተዳደርማ ሆነ ትህነግ በኩል ዝርዝር ምላሽ እንደሚወጣ በርካቶች ጠብቀው ነበር።
ይሁን እንጂ ን ከትግራይ የወጣው ምላሽ የፕሪቶሪያው ስምምነት እንደሚገባው አልተተገበረም በሚል በመንግሥት ላይ የተቃውሞ መግለጫ ብቻ የተካተተበት ነው።
ለዚህ የመንግሥት ምልሽ ትሕነግ የአጸፋ መግለጫ ሰኞ ዕለት የሰጠ ሲሆን ለክልሉ የተደረገውን 37 ቢሊዮን ብር በላይ ድጋፍ ምንም ዓይነት ዕውቅና ሳይሰጥ የፕሪቶሪያው ስምምነት እንደሚገባ እየተተገበረ ባለመሆኑ በአገሪቱ ላይ ሲያካሂድ የነበረውን የሽብር ተግባር ከማስቀጠል ዕቅድ እንዳለው የሚያሳብቅ መረጃ አሰራጭቷል።
የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳዳሪ ተደርገው በፌደራል መንግስት የተሾሙት አቶ ጌታቸው ረዳ “ፀረ-ፕሪቶሪያ አቋም የያዙ አካላት ካልተወገዱ በሀገሪቱ የሰላም ማስፈን ተግባራት ላይ የማልንባበር ይሆናል” ሲሉ በመግለሻው ላይ ገልጸዋል። ይህን ሲሉ ምን ለማለት ፈልገው እንደሆነ አልተብራራም። የትግራይ ክልልን የሚመራው ትህነግ ቢትዮጵያ በሚካሄዱ የሰላም ማስፈን ተግባራት እንደማይሳተፍ ማስጠንቀቁ ዳግም ወረራ ለመፈጸም ይሁን ለሌላ አልታወቀም፣ የፕሪቶሪያውን ስምምነት ተከትሎ ትህነግ ከኦነግ ሸኔ ጋር ቀደም ሲል የመሰረተው ጥምረት በህግ በይፋ መቋረጡን እንዳላስታወቀ፣ በአሁኑ ሰዓት ከአማራ ክልል ከተወሰኑ የጎጃም አካባቢ እንቅስቃሴ መሪዎች ጋር ግንኙነት ስለመፍጠሩ የሚወጡ መረጃዎችን እንደሚገፋባቸው ስለማሳወቁ እንደሆነ ለጊዜው ግልጽ አይደለም።
ተከታዮቹ ነጥቦች ከትሕነግ አፃፋዊ መግለጫ የተመራረጡ ይዘቶች ናቸው፤
“ከፕሪቶርያ ስምምነት አፈፃፅም ጋር በተያያዘ በኮሙኒኬሽን አገልግሎት መግለጫ ላይ የተጠቀሰውና ከትግራይ ሉዓላዊ ግዛት መረጋገጥ ጋር በተያያዘ ጉዳዩን በሪፈረንደም ለመፍታት መረዳዳት ተደርሶ ነበር በሚል የቀረበው መግለጫ የተሳሳተ…” ሲል ገልፆታል
“በፕሪቶሪያ ስምምነት መሠረት ሕገ መንግሥቱ ጉዳዩን መፍታት እንዳለበት ከስምምነት በተደረሰው መሠረት መሆን አለበት…”
ከዚህ ውጭ ጉዳዩን ለመፍታት የትግራይ ጊዜያዊ አሰተዳደርም ሆነ ፌደራል መንግሥቱ ካላቸው ሥልጣን ውጪ የሆነ ተግባር …” በማለት “ተቀባይነት የሌለዉ ነው” ብሏል
“ትክክለኛ ተፈናቃዮች ተመልሰዋል” የሚለው የመግለጫው ክፍል እጅግ አደገኛና በጉልበት የሃገራቱ ካርታ ለመቀየር የፌዴራል መከላከያ ሆነ የጎርቤት ሃገራትን አቅም ተጠቅሞ ለተደረገ አውዳሚ እንቅስቃሴ ሕጋዊ ሽፋን ለመስጠት ነው…”
“ከሚልዮን በላይ ቁጥር ያላቸው ተፈናቃዮች በአስከፊ ሁኔታ የሚኖሩት፤ በጸረ ሕዝብ እና በሕገ ወጥ አስተዳደሪዎች (የአማራ ክልል አመራሮች) አማካኝነት ነው” በማለት፣ ፌደራል መንግሥቱም ከመንበራቸው እንዲያነሳቸው ይጠብቁ እንደነበር ገልጿል። አነዚህ (የአማራ ክልል) አመራሮቹ አሁንም ሕግ አስከባሪዎች ነን ማለታቸው በፍፁም ተቀባይነት የለውም”
የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳዳር የፕሪቶሪያው ስምምነት ባልተሸራረፈ መልኩ የሚተገበርበት፤ እና የትግራይ ሕዝብ ራሱን በራሱ የማስተዳደር መብቱ በተሟላ መልኩ የሚያረጋገጥበት ሁኔታ እንዲፈጠር ፅኑ አቋሙ መሆኑን የገለፀ ሲሆን፣ ከዚህ ውጭ “ፀረ-ፕሪቶሪያ ስምምነት” አቋም የያዙ አካላትን መንግሥት የሚደግፍ ከሆነ/ካበረታታ፣ በትግራይም ሆነ በሌሎች የኢትዮጵያ አካባቢዎች ሰላም እንዲሰፍን በሚደረግ ተግባር ውስጥ ከመንግስት ጋር እንደማንተባበር እንገልፃለን ብሏል። (Esleman Abay የዓባይ ልጅ)
የትግራይ ክልላዊ ጊዜያዊ አስተዳደር።