“ከየትኛውም የኢትዮጵያ ክልል አስተማማኝ ሰላም ያለው እዚህ ነው። ለሰራተኞች እንደ ቤተሰብ ዝግጅት አድርገናል። ኑ” ሲሉ የተሰሙት አምስት መቶና ሶስት መቶ ሄክታር ሰሊጥና ማሽላ ያመረቱ ባለሃብቶች ናቸው። የዞኑ ግብርና ቢሮ ሃላፊ እንዳሉት አንድ ሚሊዮን አንድ መቶ ሃምሳ ሁለት ሺህ ኩንታል የሰሊጥ ምርት ስለሚጠበቅ ከአንድ ሚሊዮን በላይ የሰራተኛ ሃይል ያስፈልጋል።
የዞኑ አርባ በመቶ በሰሊጥ ምርት መሸፈኑን ያመለከቱት የዞኑ የግብርና ቢሮ ሃላፊ አቶ አወቀ መብራቱ ” ሰሊጥ ሲሰበሰብ በቂ የሰው ሃይልና ጥንቃቄ ስለሚሻ ይህን ባገናዘበ መልኩ አጨዳ ለመጀመር ዝግጅት ተደርጓል” ብለዋል። ከዝግጅቱ መካከልም ሰራተኞችን መቀበል ነው። ከአጎራባች ዞኖች ጋር በጋር እየተሰራ እንደሆነም አመልክተዋል።
በአማራ ቴሌቪዥን ቀርበው የተናገሩት ባለሃብቶች ዞናቸው እጅግ ሰላማዊ በመሆኑ አጨዳ ለመጀመር ለሰራተኞች ማረፊያ፣ ቀለብ፣ ትራንስፖርትና መድሃኒት ማዘጋጀታቸውን አመልክተዋል። ” ሰርተን፣ ጥሩ ምርት አግኝተን፣ ራሳችንን ጠቅመን፣ ለመንግስት የሚጠብቅብንን ከፍለን አብረን መሻሻል አላማችን ነውና መጥታችሁ ሰርታችሁ እናንተም ተጠቀሙ። እንደ ቤተሰብ ለንቀበላችሁ ዝግጁ ነን” ሲሉ ጥሪያቸውን በሚዘናጠፈውና ታይቶ በማያለቅው ማሳ ውስጥ ሆነው ጥሪ አሰምተዋል።
2014 ዓ ም የምርት ዘመን በተመሳሳይ ለሰራተኞች ቅጥር ማስታወቂያ ሲነገር የትግራይ ህዝብ ነጻ አውጪና 360ዎች በመቀባበል ” አትመዝገቡ፣ አትሂዱ፣ ወታደር አድርገው ሊማግዷችሁ ነው” በሚል በተደጋጋሚ ቅስቀሳ ማካሄዳቸው በወቅቱ ከፍተኛ ቅሬታ ያስነሳ፣ በታሪክም የማይረሳ ጠላትነት እንደሆነ ጠቅሰው አስተያየት ሲሰጡ እንደነበር ይታወሳል።
አሁን ላይ የመንግስት ተቃዋሚ ሚዲያ እየመራ ያለው ጌታቸው ሽፈራው በወቅቱ “ኢትዮ 360 በጦርነቱ ምክንያት መሬት ጦሙን አደረ ሲል ከርሞ፣ አሁን ለሰብል ስብሰባ የሰራተኛ ቅጥር ሲወጣ የህወሓትን አጀንዳ እያራገበ በህዝብ ላይ ሌላ ጦርነት ከፍቷል” በሚል ከትቦ ነበር። ጌታቸው ሽፈራው በራሱ የማህበራዊ ገጽ ሳይቀር ባሰራጨው ሰፊ አስተያየት 360ዎች “በአንድ ዞን ሚሊዮን የስራ እድል ሲፈጠር እንዲስተጓጎል እየሰሩ ነው። አርሶ አደር ሰብል እንዳይሰበስብ ቅስቀሳ ማድረግ በህዝብ ላይ ጦርነት መክፈት ነው። ሚሊዮን ወጣት ስራ እንዳይሰራ መቀስቀስ ወንጀል ነው። ያፈጠጠ የህዝብ ጠላትነት ነው” ሲል አክርሮ ማስረጃ በማስደገፍ ተቃውሞውን ገልጾ እንደነበር ይታወሳል።
ይህ እስከታተመ ድረስ በግልጽ የተሰማ የተቃውሞ ቅስቀሳ ባይኖርም ” ጎንደር ዓይናቸውን በሰሊጥ መሬት ላይ በተከሉ፣ ለሃጫቸውን በቦሎቄ ፍሬ ላይ በሚያዝረበረቡ፣ ወልቃይትን እንደ ድሬደዋ መስተዳድር ራስ ገዝ አድርገው ከዐማራ ሊለዩ በሚታትሩ ተውሳኮች የታጠረች፣ የተመረዘች፣ ጎንደር አሜሪካ ተቀምጠው ሳይደክሙ የሸዋና የጎጃም፣ የወሎና የጎንደር ፋኖዎችን በፍርፋሪ ዶላር ከፋፍለው 4 ኪሎ ለመግባት ቋምጠው በተጎለቱ ድልብ የተማሩ መሃይሞች ተጠርንፋ ያለችና እነዚህ ሾተላዮች ሊወገዱላት የሚገባት ናት” ሲል Zemedkun Bekele (ዘመዴ) በቴሌግራም ገጹ ስለጎንደር መያዝ መስማቱን ጠቅሶ ማረጋገጫ ሳይሰጥ ጽሁፍ አሰርጭቷል።
ይኸው የአማራ ትግልን ከሚመሩት ወገን የአንዱ ወገን እንደሆነ የሚገልጸው Zemedkun Bekele (ዘመዴ) ሰሞኑንን በተከታታይ “ጎንደር ባንዳ ሆነ” በሚል ሲጽፍና የጎንደርን ዝምታ ከሰሊጥ ጋር በማያያዝ ወልቃይት ራስ ገዝ እንድትሆን የሚደራደሩ ዓይነት አድርጎ ስሏቸዋል።
ወልቃይት ጠገዴ ሲቲትሁመራ የሰላም ቀጠና መሆኑንን ጠቅሰው ኮሎኔል ደመቀ ሲናገሩ ” ከመከላከያ ጋር እጅ ለጅ ሆነን እየሰራን ነው” ማለታቸውን ተከትሎ ትችት ተሰንዝሮባቸው እንደነበር ይታወሳል። ከከፍተኛ ሰቆቃ እንደተላቀቁ የሚናገሩት የውልቃይት ጠገዴ ሲቲት ሁመራ ነዋሪዎች ራሳቸውን አደራጅተው በጥብቅ ስነስርዓት ሌትና ቀን አካባቢያቸውን እንደሚጠብቁ፣ መከላከያም ያለአንዳች ስጋት የራሱን ስራ እንደሚሰራ ኮሎኔሉን የጠቀሳቸው የጀርመን ድምጽ ከወራት በፊት ማስታወቁ አይዘነጋም።
በዞኑ ከአስራ ሁለት በላይ የተላያዩ አዝርዕቶች የሚበቅሉ ሲሆን በዘንድሮው ዓመት ከሰሊጥ በተጨማሪ ከፍተኛ የማሽላ ምርት እንደሚጠበቅ ሃላፊው አስታውቀዋል። ወልቃይት ጠገዴ ሴቲት ሁመራ በአማራ ክልል እጅግ ሰፊ፣ ምቹና ለም የሆነ መሬት ያካለለ አካባቢ ነው።
- ሰው ሰራሽ ቦይ በመገንባት ቀይ ባህርን መቀላቀል የኢትዮጵያ ሌላ አማራጭ?አርተፊሻል ቦይ በመገንባት ቀይ ባህርን ወደ ኢትዮጵያ በማምጣት ኢትዮጵያ የባህር በር ሊኖራት ይችላል፤ ይህ በአለም ላይ በኢትዮጵያ የአፋር ምድር ረባዳነት የተነሳ ተፈጥሮ የሰጠው እድል ነው! በኢትዮጵያ እና በኤርትራ መካከል አርተፊሻል ቦይ በመስራት ኢትዮጵያ የወደብ ባለቤት መሆን ትችላለች፡፡ እንደዚህ አይነት አጋጣሚ ሊፈጠር የቻለው፤ የኢትዮጵያ የአፋር ቦታ ከባህር ወለል በታች እስከ 110 … Read moreContinue Reading
- ብሄራዊ ባንክ የገንዘብ ቁጥጥሩን አጠንክሮ እንደሚገፋበት አስታወቀ፤ ህገወጥ የወርቅ አዘዋዋሪዎች ላይ እርምጃ እየተወሰደ ነው– የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ አዲስ የማቋቋሚያ ረቂቅ አዋጅ አዘጋጀ በአገሪቱ የሚታየውን የዋጋ አለመረጋጋት ለመግራት የግንዘብ ስርጭት ላይ ጥብቅ ቁጥጥር በማድረግ የተጀመረው ስራ ውጤት እያሳየ መሆኑ ተመለከተ፤ ተጠናክሮ ክምሩ እንደሚሰራበትና ግሽበትን በዓመቱ መጨረሻ 20 ከመቶ ለማድረስ መታቀዱ ተሰማ። ህገወጥ የወርቅ ነጋዴዎች ላይ ጥብቅ ቁጥጥርና የማበረታቻ መደረጉ ለውጥ ቢያሳይም በቂ እንዳልሆነ ተመለከተ። … Read moreContinue Reading
- የኮሚሽኑ የቀድሞ ሠራተኞች ከ40 ሚሊየን ብር በላይ የሙስና ክስ ጋር ተያይዞ ያቀረቡት የክስ መቃወሚያ ውድቅ ሆነየአዲስ አበባ እሳት እና አደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን የቀድሞ ሠራተኞች ከ40 ሚሊየን ብር በላይ የአልባሳት ግዢ ጋር ተያይዞ በቀረበባቸው የሙስና ወንጀል ክስ ያቀረቡት የክስ መቃወሚያ ውድቅ ተደረገ። ተከሳሾቹ ያቀረቡትን የክስ መቃወሚያ ውድቅ ያደረገው የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 3ኛ የሙስና ጉዳዮች ወንጀል ችሎት ነው። የፍትሕ ሚኒስቴር የሙስና ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ዐቃቤ … Read moreContinue Reading
- መንግስት የነዳጅ ድጎማን በህገወጥ መንገድ ሲጠቀሙ ነበሩ ያላቸውን 40 ሺህ ተሽከርካሪዎች ከስርአቱ አስወጣ፣ የሰርቁትን ይከፍላሉየታለመለት የነዳጅ ድጎማን ላልተገባ ዓላማ ሲጠቀሙ የነበሩ 40 ሺህ ተሽከርካሪዎች ከድጎማ ስርዓቱ እንዲወጡና ዕዳ እንዲከፍሉ መደረጉን የፕላንና ልማት ሚኒስትር ዶክተር ፍጹም አሰፋ ገለጹ። ሚኒስትሯ ይህን ያሉት የመንግሥት የ2016 የመጀመሪያ የሩብ ዓመት አፈጻጸም በተገመገመበት ወቅት ነው። የግምገማው ተሳታፊዎች መንግሥት የነዳጅ ድጎማን ጨምሮ በርካታ የህዝብ ተጠቃሚነትን የሚያረጋገጡ ተግባራትን ማከናወኑን አድንቀው፤ ሆኖም” ድጎማው … Read moreContinue Reading
- በዓመት አምስት ሚሊዮን ቶን ሲሚንቶ የሚያመርተው ፋብሪካ ከመጋቢት በሁዋላ የሲሚንቶ ዋጋ ወደ ነበረበት የሚመልሰ ነውበቀን 10 ሺህ ቶን ሲሚንቶ እንዲያመርት እቅድ ተይዞለት በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን እንሳሮ ወረዳ ለሚ ከተማ እየተገነባ ያለውን የለሚ ናሽናል ሲሚንቶ ፋብሪካ የግንባታ በመጋቢት ወር ይጠናቀቃል። ምርቱ በተባለው ወር ሲጀምር የሲሚንቶ ዋጋ አሁን ካለበት በግማሽ እንደሚወርድ ይጠበቃል። ከመጋቢት በሁዋላ ፋብሪካው በ50 በመቶ የሲሚንቶ እጥረቱን ያስወግዳል። ኢስት አፍሪካን ሆልዲንግ ኩባንያ … Read moreContinue Reading