የአኙዋና ኑኤር ጎሳዎች ጊዜ እየጠበቀ የሚያገረሽ ግጭት ማንሳት ለማዳቸው ነው። የኑኤር አብላጫ ቁጥር ያለውና ከሱዳን እርስ በርስ ተፋላሚዎች ጋር ግንኙነት ያላቸው አመረሮችም ያሉበት በመሆኑ ብዙ ጊዜ የግጭቱ መነሻዎች እነሱ ናቸው። ከጋምቤላ የተሰማው ለበርካቶች ሞትና ንብረት ውድመት ምክንያት የሆነው አዲሱ ግጭት ተዋንያኖቹ ለህግ እንደሚቀርቡ፣ መከላከያ ጸቡን አብርዶ የማደን ስራ እየሰራ መሆኑንን ነው።
የኮሙኒኬሽን ሃላፊውን ጠቅሶ ጀርመን ድምጽ እንዳለው ቀስቃሾቹ ባለስልጣናት እነማን እንደሆኑ እየተጣራ ነው። የደረሰውም ጉዳይ ሰፊ ሲሆን አሁን ላይ መከላከያ በሁሉም ወረዳዎች ተሰማርቶ እያረጋጋ ነው። ግጭቱ ቆሞ ስጋት ላይ ያሉ አካባቢዎች ሙሉ በሙሉ ሰላም እስከሚሆኑ የሰዓት እላፊ ገደብ መጣል አስፈልጓል። ዲ ደብሊው ዘገባ ያንብቡ
የሰዓት እላፊ ገደቡ የተቀመጠው ሰሞኑን በክልሉ በተከሰተው የጸጥታ ችግር ምክንያት እንደሆነ የክልሉ ኮሙኒኬሽን አስታውቋል። የጽ/ቤቱ ኃላፊ አቶ ኡገቱ አዲንግ ለዶቼቬለ እንደተናገሩት ሰሞኑን በክልሉ በተከሰተው የጸጥታ ችግር የሰዎች ህይወት ማለፉን ተናግረዋል፡፡ በሰው እና ንብረት ላይ የደረሰው የጉዳት መጠን እየተጣራ እንደሚገኝም አክለዋል፡፡
በጋምቤላ ክልል ሰሞኑን በተከተሰው የጸጥታ ችግር በሰው ህይወት እና ንብረት ላይ ከፍተኛ ጉዳት መድረሱን የክልሉ መንግስት አስታውቋል፡፡ የጸጥታ ችግሩን ለመቆጣጠር እንዲያመች የሰዓት ዕላፊ ገደብ መጣሉን የክልሉ ኮሙኒኬሽን ጉዳዩች ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ኡገቱ አዲንግ ለዶቼቬለ ተናግረዋል፡፡ ከትናንት ማታ ጀምሮ ተግባራዊ በተደረገው የሰዓት እላፊ ከምሽቱ 1፡00 ሰዓት እስከ ንጋቱ 12፡00 ከተፈቀደላቸው የጸጥታ ሐይሎች ውጪ ሰው እና ተሽከርካሪ መንቀሰቃስ እንደማይችል ገልጸዋል፡፡ የሰዓት እላፊ ገደቡ ላልተወሰነ ጊዜ የሚቆይ ነው ያሉት ኃላፊው ሰሞኑን “ጨለማን ተገን አደርገው የሚንቀሳቀሱ የታጠቁ ቡድኖች” ጉዳት ማድረሳቸውን ተናግረዋል፡፡ በተከሰተው ግጭት በኢታንግ ልዩ ወረዳ በሰው እና ንብረት ላይ ጉዳት መድረሱን ገልጸው የጉዳት መጠኑ እየተጣራ ነው ብለዋል፡፡ ያነጋርናቸው የጋምቤላ ከተማ ነዋሪዎች ከባለፈው ሰኞ አንስቶ የጸጥታ ችግር ተባበስቦ መቆየቱ እናን ተቋማት ዝግ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡
የጋምቤላ ክልል መንግስት ካቢኔ የክልሉን የጸጥታ ሁኔታ አስመልክቶ አስቸካይ ጉባኤ ካደረገ በኃላ የሰዓት እላፊ ገደቡ መጣሉን አመልክቷል፡፡ የሰዓት እላፊ ገደቡ የተቀመጠው ሰሞኑን በክልሉ በተከሰተው የጸጥታ ችግር ምክንያት እንደሆነም የክልሉ ኮሙኒኬሽን ጉዳዩች ጽፈት ቤት አመልክተዋል፡፡ የጋምቤላ ክልል ኮሙኒኬሽን ጉዳዩች ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ኡገቱ አዲንግ በሰጡን ማብራሪያ ሰሙኑን በክልሉ በተከሰተው የጸጥታ ችግር የሰዎች ህይወት ማለፉን ተናግረዋል፡፡ በሰው እና ንብረት ላይ የደረሰው የጉዳት መጠን እየተጣራ እንደሚገኝም አክለዋል፡፡ በአሁኑ ጊዜ የፈደራል እና የክልል የፀጥታ ኃይሎች ተጨማሪ አደጋ እንዳይከሰት በየወረዳው ተሰማርተው እንደሚገኙም ለዲዳብሊው አብራርተዋል፡፡ ለዘመናት አብሮ የኖረ ማህበረሰብን ወደ ግጭት እንዲያመራ ያደረጉ እና በድርጊቱ የተሳተፉ የክልሉ አመራሮች እንዳሉም ገልጸዋል፡፡ በድርጊቱ የተሳተፉ አመራሮች ጉዳይ ተጣርቶ ህጋዊ እርምጃ እንደሚወሰድም አመልክተዋል፡፡ጋምቤላ ውስጥ የሙርሌ ጎሳ ታጣቂዎች ጥቃት
የጋምቤላ ከተማ ነዋሪ አቶ ማሙሸት ደረሰ ከባለፈው ሰኞ አንስቶ በተለያዩ ቦታዎች ላይ ግጭት መከሰቱን ተናግረዋል፡፡ በገበያ ስፍራ በዝርፍያ የተሰማሩ ግለሰቦችም እንደነበሩ አክለዋል፡፡ በገጠርማ ስፍራዎች ደግሞ ቤቶች መቃጠላቸውን እና ቁጥራቸው በውል ያልታወቁ ነዋሪዎች ላይ የሞት እና የመቁሰል አደጋ መድረሱን ተናግረዋል፡፡ በክልሉ የስደተኞች መጠለያ ውስጥ የሚኖሩ ግለሰቦችም
በግጭት ውስጥ መሳተፋቸውን የገለጹት ነዋሪው ግጭቱ የብሔር መልክ ያለው እና በአካባቢው አብሮ በሚኖሩ የአኙዋና ኑኤር ብሔረሰብ መካከል የተፈጠረ አለመግባባት እንደሆነም አብራርተዋል፡፡ በክልሉ እንደ ላረ እና ኢንታግ አካባቢ አሁንም ከፍተኛ ስጋት መኖሩን ጠቀመዋል፡፡ከማክሰኞ አንስቶ የመስሪያ ቤቶችና የንግድ ተቋማት ዝግ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡የጋምቤላ ነጻነት ግንባር ሙሉ በሙሉ ከትጥቅ ትግል መውጣቱን ዐስታወቀ
የክልሉ ኮሙኒኬሽን ትናንት ይፋ ባደረገው መረጃ የመንግስት ሰራተኞች እና ተቋማት ከዛሬ ጀምሮ መደበኛ ስራቸውን እንዲጀምሩ ውሳኔ ማሳለፉን ጠቅሷል፡፡ ህገ ወጥ የጦር መሳሪያ እና ማንኛውንም ድምጽ አልባ መሳሪያ ይዞ መንቀሳቀስ እንደማይችል የክልሉ መንግስት ገልጸዋል፡፡ ይህን ተላልፎ ይዞ የተገኘ ግለሰብ እርምጃ እንደሚወሰድበትም ተጠቁሟል፡፡ በግጭቱ ለደረሰው የሰው ህይወት ህልፈትና ንብረት ውድመት የክልሉ መንግስት የተሰማውን ጥቅል ሀዘን ገልጸዋል፡፡
ጀርመን ድምጽ እንደዘገበው
- ሰው ሰራሽ ቦይ በመገንባት ቀይ ባህርን መቀላቀል የኢትዮጵያ ሌላ አማራጭ?አርተፊሻል ቦይ በመገንባት ቀይ ባህርን ወደ ኢትዮጵያ በማምጣት ኢትዮጵያ የባህር በር ሊኖራት ይችላል፤ ይህ በአለም ላይ በኢትዮጵያ የአፋር ምድር ረባዳነት የተነሳ ተፈጥሮ የሰጠው እድል ነው! በኢትዮጵያ እና በኤርትራ መካከል አርተፊሻል ቦይ በመስራት ኢትዮጵያ የወደብ ባለቤት መሆን ትችላለች፡፡ እንደዚህ አይነት አጋጣሚ ሊፈጠር የቻለው፤ የኢትዮጵያ የአፋር ቦታ ከባህር ወለል በታች እስከ 110 … Read moreContinue Reading
- ብሄራዊ ባንክ የገንዘብ ቁጥጥሩን አጠንክሮ እንደሚገፋበት አስታወቀ፤ ህገወጥ የወርቅ አዘዋዋሪዎች ላይ እርምጃ እየተወሰደ ነው– የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ አዲስ የማቋቋሚያ ረቂቅ አዋጅ አዘጋጀ በአገሪቱ የሚታየውን የዋጋ አለመረጋጋት ለመግራት የግንዘብ ስርጭት ላይ ጥብቅ ቁጥጥር በማድረግ የተጀመረው ስራ ውጤት እያሳየ መሆኑ ተመለከተ፤ ተጠናክሮ ክምሩ እንደሚሰራበትና ግሽበትን በዓመቱ መጨረሻ 20 ከመቶ ለማድረስ መታቀዱ ተሰማ። ህገወጥ የወርቅ ነጋዴዎች ላይ ጥብቅ ቁጥጥርና የማበረታቻ መደረጉ ለውጥ ቢያሳይም በቂ እንዳልሆነ ተመለከተ። … Read moreContinue Reading
- መንግስት የነዳጅ ድጎማን በህገወጥ መንገድ ሲጠቀሙ ነበሩ ያላቸውን 40 ሺህ ተሽከርካሪዎች ከስርአቱ አስወጣ፣ የሰርቁትን ይከፍላሉየታለመለት የነዳጅ ድጎማን ላልተገባ ዓላማ ሲጠቀሙ የነበሩ 40 ሺህ ተሽከርካሪዎች ከድጎማ ስርዓቱ እንዲወጡና ዕዳ እንዲከፍሉ መደረጉን የፕላንና ልማት ሚኒስትር ዶክተር ፍጹም አሰፋ ገለጹ። ሚኒስትሯ ይህን ያሉት የመንግሥት የ2016 የመጀመሪያ የሩብ ዓመት አፈጻጸም በተገመገመበት ወቅት ነው። የግምገማው ተሳታፊዎች መንግሥት የነዳጅ ድጎማን ጨምሮ በርካታ የህዝብ ተጠቃሚነትን የሚያረጋገጡ ተግባራትን ማከናወኑን አድንቀው፤ ሆኖም” ድጎማው … Read moreContinue Reading
- በዓመት አምስት ሚሊዮን ቶን ሲሚንቶ የሚያመርተው ፋብሪካ ከመጋቢት በሁዋላ የሲሚንቶ ዋጋ ወደ ነበረበት የሚመልሰ ነውበቀን 10 ሺህ ቶን ሲሚንቶ እንዲያመርት እቅድ ተይዞለት በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን እንሳሮ ወረዳ ለሚ ከተማ እየተገነባ ያለውን የለሚ ናሽናል ሲሚንቶ ፋብሪካ የግንባታ በመጋቢት ወር ይጠናቀቃል። ምርቱ በተባለው ወር ሲጀምር የሲሚንቶ ዋጋ አሁን ካለበት በግማሽ እንደሚወርድ ይጠበቃል። ከመጋቢት በሁዋላ ፋብሪካው በ50 በመቶ የሲሚንቶ እጥረቱን ያስወግዳል። ኢስት አፍሪካን ሆልዲንግ ኩባንያ … Read moreContinue Reading
- አዲስ አበባ – ሙስና በገሃድ፤ የትራንስፖርት ፣ የመሬት፣ የካርታ፣ የግንባታ ፍቃድ ፣ የመታወቂያ … አገልግሎቶች ምሬት” የጸረ ሙስና ኮሚሽን ራሱ ሌላ መረማሪ ተቋም ሊበጅለት ይገባል” እስኪባል ድረስ ተቋሙ የነተበ ስለመሆኑ ያቋቋሙት አቶ መለስ በህይወት እያሉ የተሰጠ አስተያየት ነበር። ዛሬም ድረስ ያው ነው። ህዝብ በገሃድ የሚያየውን ሰላዮቹ “አልታየንም” ሲሉ የሚነከባከቡት ሌብነት ጉዳይ የብልጽግና ፈተና ሆኗል። በዚህ አያያዝ ፓርቲው ራሱን በራሱ ሊበላ እንደሚችል እየተጠቆመ ነው። በተቁማት ውስጥ … Read moreContinue Reading
- ህገወጥ የውጭ ገንዘብ አምራቾች ተያዙ፤ ማንነታቸውና ስማቸው መደበቁ ጥርጣሬ ፈጥሯልበኢትዮጵያ የውጭ ምንዛሬ አጣቢዎችን ማንነት ለማወቅ ከባህር ማዶ ቢሮ ከፍተው ዶላር የሚሰበስቡትን ከመጠርሪያ ስማቸው በመነሳት መለያየት ቀላል ነው። በውጭ አገር ሆነው ፖለቲካ በመቀመርና ለፖለቲካ ቅመራው እርዳታ በመጠየቅ የዲጂታል ለማኝ የሆኑት ቢያንስ ይህን ስራ ቢሰሩ እንደሚሻላሸው ምክር የሚሰጡት ስራው እጅግ ከፍተኛ ገንዘው ወደ ሌላ አገር እያሻገረ በመሆኑ ነው። በዚሁ የምንዛሬ አጠባ … Read moreContinue Reading