“ድርጅታችን ኦቪድ ግሩፕ በሀሰተኛ የመረጃ እና በስም ማጥፋት በተሳተፉ አካላት ላይ ክስ መስርቷል” ሲል በላከልን መግለጫ አመልክቷል። የድርጅቱን ዓላማ፣ መርህና ራዕይ እንዲሉም ያከናወናቸውን ተግባራት አስረድቶ ” ስሜ ጠፍቷል” ሲል ክስ መመስረቱን ገልጿል።
“… ያለስማችን ስም ለሰጡን፣ ያለተግበራችን በሐሰት በድርጅታችን ስምና ብራንድ ላይ ሐሰተኛ መረጃ ባቀረቡና ባሳራጩ በአገር ውስጥና በውጭ በሚገኙ ግለሰቦችና ሚዲያዎች ላይ አስፈላጊውን መረጃ አሰባስቦ በውጭ በሚገኙ ድርጅቶቹ በኩል ክስ የመሰረተ መሆኑንም ያሳውቃል” ያለው የድርጅቱ መግለጫ፣ “ጉዳዩንም ድርጅታችን በሕግ ተከታትሎ ለማስወሰን በአሜሪካ ፣ በጀርመንና በእስራዔል አገራት በውጭ በሚገኙ አጋር ደርጅቶቹ በኩል ጠበቆችን ቀጥሮ ክትትል እያደረገ ይገኛል” ብሏል።
ድርጅቱ በአማራ ክልል የተቀሰቀስወን ጦርነት ተከትሎ በተለያዩ የኦሮሚያ አካባቢዎች ወይም ከተሞች የማጎሪያ ካምፖችን የሚሰራ ብቸኛ ተቋም መሆኑ ተጠቅሶ በስፋት መረጃ ሲሰራጭ ሰንብቷል። ይህንኑ መረጃ የተቀባበሉ ድርጅቱን ሲከሱና በወንጀለኛነት ሲፈርጁትም ነበር። ይህንኑ መረጃ “የስም ማጥፋት ነው” ሲል በተጠቀሱት አጋር ኩባንያዎቹ አማካይነት ክስ መመስረቱን ከማስታወቁ ድርጅቱ በምን ያህል ኪሳራና መጠን ክስ እንደሚመሰርት ይፋ አላደረገም። መግለጫው ከስር ያለው ነው።
ከኦቪድ ግሩፕ ሐሰተኛ መረጃን አስመልክቶ የተሰጠ መግለጫ
ድርጅታችን ኦቪድ ግሩፕ በሀሰተኛ የመረጃ እና በስም ማጥፋት በተሳተፉ አካላት ላይ ክስ መስርቷል፡፡
በኮንስትራክሽን ዘርፉ ለ20 ዓመታት በአገራችን የተለያዩ አካባቢዎች ግንባታን በማከናወን ከፍተኛ ልምድ ያካበተው ደርጅትቻችን በ2006 ዓ.ም በርካታ ደርጅቶችን አቅፎ ወደ ኦቪድ ግሩፕ ማደግ ችሏል፡፡ ግሩፑ በአሁኑ ሰዓት የ30 የማኑፈክቸሪንግ ፣የትራንስፖርትና ትምህርት ዘርፍ ላይ የተሰማሩ ግዙፍ ደርጅቶችና 12 የኮንስትራክሽን ድርጅቶች ጥምረትን እውን ለማድረግ ”Our Vision is Development ወይም ራዕያችን ልማት ነው” በሚል መሪ ቃል በትጋት እየሰራ ያለ ሀገር-በቀል ተቋም ነው፡፡
በስራ ላይ ያሉትም ሆነ በመቋቋም ላይ ያሉት ተቋማት በድርጅቱ ውስጥ ከፍተኛ ለውጥ ለማምጣት በሚተጉ ሰራተኞችን በባለቤትነት የሚያቅፉና የሚተዳደሩ ሲሆን ይኸውም ድርጅታችን ኦቪድ ግሩፕን በአይነቱ ልዮ ያደርገዋል።
ለ 20 ዓመታት ያክል በርካታ ግንባታዎችን ሲያከናውን የቆየ ሲሆን በተለይ በኮምፕረስ እርዝ ብሎክ ፣በማግኒዥየም ቦርድ እና ፓኔሎች፣ የፕላስቲክ ፎርም ወርክ (ሞላዲ) ፣ላይት ጌጅ እስቲል፣ኬ-ስፓን ካስት ኢን ሲቱ ኮንክሪት እና ኩምካንግ አሉምኒየም ፎርም ወርክ ቴክኖሎጂን በመጠቀም ግንባታዎችን በማከናወን በአገራችን የመጀመሪያው በመሆን ሰፊ ተቀባይነት አግኝቷል፡፡ ድርጅታችን ኦቪድ ግሩፕ ሥራዎቹን በአገር ውስጥ ካሉና እና በውጭ አገራት ከሚገኙ ስመጥር ደርጅቶች ጋርም ጥምረት ያለው በመሆኑ ዓለምዓቀፋዊ ቅርጽና ተወዳዳሪነት መርህን መሰረት አድርጎ የተቋቋመ ነው፡፡ ተቋማችን ዓለምዓቀፍ ድርጅቶች ጋር ጥምረት ለመመሰረት ያስቻለውም ከማንኛውም የፖለቲካ እንቅስቃሴ፣ ተሳትፎና ድጋፍ የገለልተኛነት መርሆችን በተግባር አክብሮ የሚያንቀሳቀስ በመሆኑ ነው፡፡
ኦቪድ ግሩፕ በአገር ውስጥ እና ከውጭ አገራት ስመጥር ኩባንያዎች ጋር ያለውን ጥምረት በመጠቀም በመኖሪያ ቤት ግንባታ የሚስተዋለውን የፍጥነት እና የጥራት ችግር ዘመናዊ ቴክኖሎጂን በመጠቀም ፍጥነት እና ጥራትን በመጨመር በከተሞች እየታየ ያለውን ከፍተኛ የሆነ የመኖሪያ ቤት ችግር ለመፍታት በተግባር የተረጋገጠ መፍትሄ ይዞ የመጣ ሀገር በቀል ደርጅት ነው፡፡ በተለይ በአዲስ አበባ ከተማ በከፍተኛ በጀት ከ60 ሺህ ቤቶች በላይ ያያዘ ዘመናዊ ከተማ ለመገንባት ተግባራዊ እንቅስቃሴ እያከናወነ ያለ ድርጅት መሆኑንም ለማሳወቅ እንወዳለን፡፡
የድርጅታችን ራዕይ እንደ ስያሜያችንና መሪ-ቃላችን የኢትዮጵያን ፍጹም እድገትና ልማት እንዲሁም ዓለምዓቀፋዊ ጥምረት እንዳለው ደርጅት ደግሞ የገለልተኝት መርሆችን አክብሮና አውቆ እንደሚሰራ ለማንም አካል ግልጽ ሆኖ እያለ የደርጅታችን ስምና ብራንድ ላይ ጉዳት ለማድረስ ሐሰተኛ የማህበራዊ ሚዲያ ዘመቻ በአንዳንድ አካለት ተስተውለዋል፡፡
ለዚህም ድርጅታችን በቸልተኝነት ያለስማችን ስም ለሰጡን፣ ያለተግበራችን በሐሰት በድርጅታችን ስምና ብራንድ ላይ ሐሰተኛ መረጃ ባቀረቡና ባሳራጩ በአገር ውስጥና በውጭ በሚገኙ ግለሰቦችና ሚዲያዎች ላይ አስፈላጊውን መረጃ አሰባስቦ በውጭ በሚገኙ ድርጅቶቹ በኩል ክስ የመሰረተ መሆኑንም ያሳውቃል፡፡ ጉዳዩኑም ድርጅታችን በሕግ ተከታትሎ ለማስወሰን በአሜሪካ ፣ በጀርመን እና በእስራዔል አገራት በውጭ በሚገኙ አጋር ደርጅቶቹ በኩል ጠበቆችን ቀጥሮ ክትትል እያደረገ ይገኛል፡፡
ድርጅታችን ኦቪድ ግሩፕ በመልካም ስሙና ተግባሩ የሚታወቅና ማህበራዊ ኃላፊነቱን ለመወጣት ከ300 ሚሊየን ብር በላይ መድቦ 2 ሺህ እናቶችን ተጠቃሚ የሚያደርግ በቀን እስከ 288 ሺህ እንጀራን የሚጋግር የእንጀራ ፋብሪካን ጨምሮ ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው ወገኖቻችን በአዲስ አበባ ከተማ በሰባት የተለያዩ ቦታዎች እንዲሁም በአማራ ክልል በባህርዳርና በማንኩሳ ከተማ የመኖሪያ ቤት በመገንባት፣ አነስተኛ ገቢ ያላቸውን የማህበረሰባችንን ክፍሎች የምግብ አቅርቦት በማድረግ ሰፊ ድጋፍ እያደረገ ያለ ደርጅት ሲሆን ይህንኑ ተግባርም አጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል፡፡
የድርጅታችንን መልካም ስምና ተግባር እንዲሁም ጠንካራ የገለልተኝነት መርሆችን የሚያውቁ ቅን ግለሰቦች መረጃው ከድርጅታችን ጋር ፈጽሞ ግንኙነት የሌለው ሐሰተኛ መረጃ መሆኑን ተረድተው ድርጊቱን በጽኑ በማውገዛቸው ተቋማችን ልባዊ ምስጋናውን ማቅረብ ይፈልጋል፡፡
ኦቪድ ግሩፕ (ራዕያችን ልማት ነው)
OVID GROUP (Our Vision Is Development)
- የበርሊን ማራቶን ባለማዕረግ ትግስት እነ ዱቤ ጂሎ ቢሳተፉ ታዝረከርካቸው ነበርበማራቶን ከሁለት ደቂቃ በላይ ማሻሻል እጅግ የሚደነቅና ያልተለመደ ነው። ባለሙያዎቹ ወይም አሰልጣኞቹ የሮጠችበትን ፍጥነት በሰዓትና ርቀት ከፋፍለው ቢያቀርቡት ምን አልባትም ወንዶችን የሚገዳደር ፍጥነት ተጠቅማ ሮጣለች። የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ተቴክኒክ ዳይሬክተርና የአትሌቶች ኮሚሽን ሰብሳቢ የነበሩት የዛሬው የተከበሩ ዱቤ ጅሎ አይነቱን ሯጮችን አዝረክርኮ ማሸነፍ የሚያስችላትን ሃይል አሳይታለች። የበርሊና ባለ ማዕረግ ትዕግስት!! ተግስት … Read moreContinue Reading
- የባህር ዳር ነዋሪዎች- ኢትዮጵያን ዜጎች በሁሉም ቦታ እኩል የሚስተናገዱባት ሀገር ማድረግ ይገባልየባህር ዳር ነዋሪዎች የሕዝብን ጥያቄ የመፍታት አቅም፣ ፍላጎት እና ቅንነት ያለው አመራር በመፍጠር ሕዝብን መካስ እንደሚያስፈልግ፣ ኢትዮጵያ በዘር ከመገፋፋት እና ከመጠቃቃት ነጻ የኾነች ፣ዜጎች በሁሉም ቦታ እኩል የሚስተናገዱባት ሀገር እንድትኾን ማድረግና የፌዴራል መንግሥት የአማራ ሕዝብ ኅብረ ብሔራዊ እና ልማት ወዳድ እንጅ ጦርነትን የማይፈልግ መኾኑን በውል በመገንዘብ የሕዝቡን ተዘዋውሮ የመሥራት እና … Read moreContinue Reading
- ለወልቃይት ጠገዴ ሴቲት ሁመራ አንድ ሚሊዮን የጉልበት ሰራተኛ ይፈለጋል፤ ከአንድ ነጥን አንድ ሚሊዮን ኩንታል በላይ ሰሊጥ ይጠበቃል“ከየትኛውም የኢትዮጵያ ክልል አስተማማኝ ሰላም ያለው እዚህ ነው። ለሰራተኞች እንደ ቤተሰብ ዝግጅት አድርገናል። ኑ” ሲሉ የተሰሙት አምስት መቶና ሶስት መቶ ሄክታር ሰሊጥና ማሽላ ያመረቱ ባለሃብቶች ናቸው። የዞኑ ግብርና ቢሮ ሃላፊ እንዳሉት አንድ ሚሊዮን አንድ መቶ ሃምሳ ሁለት ሺህ ኩንታል የሰሊጥ ምርት ስለሚጠበቅ ከአንድ ሚሊዮን በላይ የሰራተኛ ሃይል ያስፈልጋል። የዞኑ አርባ … Read moreContinue Reading
- የጎንደርን ከተማ ምን አይነት ተኩስ እንደሌለ ተገለጸ፤ ጎንደር ተይዛለች ተብሎ ነበር“ጎንደር ከተማን ሙሉ በሙሉ ይዘናታል” ሲሉ ስማቸው እንዳይገለጽ ጠይቀው ለጀርመን ድምጽ መረጃ በሰጡ የአማራ ሕዝባዊ ኃይል ፋኖ ቃል አቀባይ አየር ማረፊያውን ሆን ብለው እንዳልያዙ አመልክተዋል። እሳቸው ተናገሩ የተባለው በጀርመን ድምጽ እየተሰማ በለበት ሰዓት በተመሳሳይ የጎንደር ከተማ አስተዳደር ውጊያ መደረጉን ሳያስተባብል ከተማዋን ለመያዝ የገባው ሃይል መደምሰሱን አሃዝ ጠቅሶ አመልክቷል። አገር መከላከያም … Read moreContinue Reading
- “የሞተው ባልሽ ገዳዩ ወንድምሽ፣ሀዘንሽ ቅጥ አጣ ከቤትሽ አልወጣ”የሞተው ባልሽ ገዳዩ ወንድምሽ (ሀዘንሽ ቅጥ አጣ ከቤትሽ አልወጣ) የሚለው የቆየ ተረት ልብን የሚያደማ ኩነትን ማሳያ ነው። እቺ መከረኛ ሚስት ባልዋ በእናቷ ልጅ ወንድሟ ተገደለ። ሟች ባል፣ ገዳይ ወንድም … ኢህአፓ “ሃይማኖት ነው” በሚል ሲገልጸው በነበረው ትግል በቀይና ነጭ ሽብር ስም እናቶች የወላድ መካን ሆነዋል። ጧሪ ያጡና ባዶ ቤት ሃዘን … Read moreContinue Reading