የአፍሪካ ህብረት ተጨማሪ 400 ሚሊየን የኮሮና ቫይረስ ክትባት እንደሚያቀርብ አስታወቀ

የአፍሪካ ህብረት ለአባል ሃገራቱ የሚሆን ተጨማሪ 400 ሚሊየን መጠን ያለው የኮሮና ቫይረስ ክትባት እንደሚያቀርብ የአፍሪካ በሽታ መከላከያ እና መቆጣጠሪያ ማዕከል /ሲዲሲ/ አስታወቀ፡፡
የማዕከሉ ዳይሬክተር ጆን ንከንጋሶንግ ክትባቱ የሚገኘው የኦክስፎርዱን አስትራዜኒካ ቀመር በመጠቀም ክትባት ከሚያመርተው ሴረም ከተሰኘ የህንድ ተቋም ነው ብለዋል፡፡
ህብረቱ ከዚህ ቀደም 270 ሚሊየን መጠን ያለው የኮሮና ቫይረስ ክትባት ለአባል ሃገራቱ እንደሚያቀርብ መግለጹ ይታወሳል፡፡ የአሁኑ 400 ሚሊየን መጠን ያለው የኮሮና ቫይረስ ክትባት ሲታከልበት ለአባል ሃገራቱ መልካም ዜና መሆኑን ነው ዳይሬክተሩ የገለጹት፡፡
አፍሪካ 60 በመቶ የሚሆነው ህዝቧን የመከላከል አቅም ለማዳበር 1 ነጥብ 5 ቢሊየን መጠን ክትባት እንደምትፈልግ የተገለጸ ሲሆን ለዚህም ከ7 እስከ 10 ቢሊየን ዶላር ያስፈልጋል ተብሏል፡፡
የአፍሪካ ህብረት ከዚህ ቀደም አፍሪካውያን ከሚያዝያ እስከ ሰኔ ባለው ጊዜ ውስጥ ቢያንስ 50 ሚሊየን መጠን ያለው ክትባት እንደሚያገኙ መግለጹ ይታወሳል፡ እስካሁን ከአባል ሃገራት መካከል ሞሮኮ፣ ግብጽ፣ ሲይሼልስ እና ጊኒ ዜጎቻቸውን መከተብ ጀምረዋል፡፡
(ኤፍቢሲ)
Related posts:
በመኪና አደጋ አራት የጤና ባለሙያዎችን ህይወት አለፈ
የሞት ቅጣት የሚያሰጋቸው ጀማል እና ሀሰን
"ሃያ አንዱ ማኅበራዊ ሕግጋት ●●●
የአቅመ ደካሞችን ጣሪያ መድፈንም ያስወግዛል?
በኦሮሚያ ቦረና ዞን - ገበሬዎች ራሳቸው ሞፈር እየጎተቱ እያረሱ ነው
ከደሴ ከተማ ቤተ-እምነቶች እና ህዝባዊ ተቋማት ህብረት የተሰጠ መግለጫ
«በትግራይ መንግሥት እርዳታ በትክክል ለተጠቃሚዎች እንደሚደርስ ይቆጣጠራል»
የአስር ዓመት ልጅን በሽተኛ በማስመሰል በሶስት ሚኒባስ ተደራጅተው ሲለምኑ የነበሩ ተያዙ
ከ33 ሺህ በላይ ሕገ ወጥ ነጋዴዎች ላይ እርምጃ ተወሰደ
“ምግቤን ከጓሮዬ”
“ባለፉት 6 ወራት ብቻ 231 ሀሰተኛ የሰነድ ማስረጃዎች ተይዘዋል”
የረሀብ ተጋላጭነቷን ለመቀነስ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ እየሰራ መሆኑን ግብርና ሚኒስቴር ገለጸ
ሥርዐት አልባው ንግድ እና ስጋት የፈጠረው የኑሮ ውድነት!
የስንዴ ምች ዓለምን እያሻት ነው - የዩክሬኑ ጦርነት
« የትግራይ ህዝብ የማዳበርያና የምርጥ ዘር ዕዳ ክፈሉ ማለት ጭካኔ ነው»