ሶስቱም የትግራይ ክልል የፕሪሚየር ሊግ ክለቦች በ2014 የውድድር ዘመን በፕሪሚየር ሊጉ የመሳተፍ ፍላጎት እንዳላቸው አሳወቁ። እግር ኳስ ፌዴሬሽን በሚችለው ሁሉ ድጋፍ እንደሚያደርግ አስታውቋል። የክለቦቹ ውሳኔ የበረሃውን ፖለቲካ በአገርም ሆነ በውጭ ውሃ እንዲደፋበት ሰልመሚያደርገው ከወዲሁ በክለቡ አመራሮች ላይ ዘመቻ እንዳይጀመር ተሰግቷል።
ዜናውን ኢቢሲ ይፋ ማድረጉን ተከትሎ የነጋገርናቸው እንዳሉን ከሆን ተቃውሞ መነሳቱ አይቀርም። ” ኳስ ሰፊ መሰረቱ ማህበራዊ ግኝኙነት ነውና በትግራይ የእግር ኳስ ውድድር ከተጀመረ የበረሃው ፖለቲካ ላይ ትልቅ አሉታዊ ተጽዕኖ ስለሚኖረው፣ በዓለም ዓቀፍ ደራጃ ስፖርት የሰላም ማሳያ ስለሆን እይታ ስለሚቀይር የበረሃው ሃይል ደጋፊ ሚዲያዎች ዘመቻ እንደሚጀምሩ ይጠበቃል” ሲሉ የአንዱ ክለብ አስልጣኝ የነበሩ ነግረውናል።
የፕቲማየር ሊጉ ውድድር በዲኤስ ቲቪ በቀጥታ ለዓለም እይታ ስለሚበቃ እንደርታ፣ መቀሌና አዲግራት ትግራይ ላይ ሲጫውቀቱ ማሳየት በዓለም ዓቀፍ ደረጃ የሚፈጥረው ስዕል ከፍተኛ በመሆኑ አዲሱ ይክልሉ ጊዚያዊ አስተዳደር ድጋፍ ሊያደርጉ እንደሚችሉ ተጠቁሟል። የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴና አትሌቲክስ ፌዴሬሽን፣ እንዲሁም በቂ ካፒታል ያላቸው ክለቦች ድጋፍ ሊያደርጉ እንደሚገባም አስተያየት ሰጪው ተናግረዋል።
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ዛሬ ከ3ቱም የትግራይ ክልል የፕሪሚየር ሊግ ተሳታፊ ክለቦች ጋር ስለ ቀጣይ የውድድር ዘመን ተሳትፏቸው ውይይት አድርጓል።
በውይይቱ ክለቦቹ በአሁኑ ወቅት ያሉበትን ነባራዊ ሁኔታ ያስረዱ ሲሆን ወደ ውድድር ለመመለስ ፋይናንስ ትልቅ ማነቆ እንደሚሆንባቸው አስረድተዋል።
ከውይይቱ ያገኟቸውን የሀሳብ ግብዓቶች ወስደው ወደ ክለቦቻቸው በመመለስ፣ ከደጋፊዎቻቸው እና ከክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ጋር በመነጋገር በአጭር ጊዜ ውስጥ የመጨረሻ ውሳኔያቸውን እንደሚያሳውቁ ገልጸዋል።
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን በኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽን በኩል የ600 ሺህ ብር ድጋፍ ማድረጉ የተገለፀ ሲሆን፣ ለዚህም የክልሉ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ምስጋናውን አቅርቧል።
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንም ክለቦቹ ወደ ውድድር እንዲመለሱ ለማድረግ በሚችለው ሁሉ ለማገዝ ዝግጁ መሆኑን መግለፁን ከፌዴሬሽኑ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
- አፍሪቃ ህብረት ምን አሰጋውና “ገንዘቤን ወደ ሌላ አገር ለማዛወር እያሰብኩ ነው” ሲል ተንሿከከ፤ የጾምና የፍስክ ዜናዎችባንኩ የክፍያ ሰነድ ቀረበለት። ማጣሪያ ጥያቄ ለህብረቱ አቀረበ። ሃሰት ሆኖ ተገኘና ፖሊስ ተጠርጣሪዎቹን ያዘ። ጉዳዩ ወደ ህግ አመራ።… Read more: አፍሪቃ ህብረት ምን አሰጋውና “ገንዘቤን ወደ ሌላ አገር ለማዛወር እያሰብኩ ነው” ሲል ተንሿከከ፤ የጾምና የፍስክ ዜናዎች
- የኢትዮጵያ ኤልክትሪክ ኃይል 300 ቢሊዮን ብር የንግድ ባንክ ዕዳ አለብኝ አለ፤ ዕዳውና የክፍያው ጫና እንደከበደውም አስታውቋልየኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከንግድ ባንክ 300 ቢሊዮን ብር ዕዳ እንዳለበት ተገለጸ። የዕዳ ጫናውን ለማቃለል የባንክ ወልዱም ጭምር ተፅእኖ… Read more: የኢትዮጵያ ኤልክትሪክ ኃይል 300 ቢሊዮን ብር የንግድ ባንክ ዕዳ አለብኝ አለ፤ ዕዳውና የክፍያው ጫና እንደከበደውም አስታውቋል
- ዋና ዋና የሽግግር ፍትህ ፖሊሲ ይዘቶች – ሲጨመቁመግቢያ ሽግግር ፍትህ ጉልህ የመብት ጥሰቶች በተፈፀመባቸው ሀገራት ተጠያቂነትን ለማስፈን እና ተበዳዮችን ለመካስ ጥቅም ላይ ሲውል ቆይቷል፡፡ በሀገራችንም… Read more: ዋና ዋና የሽግግር ፍትህ ፖሊሲ ይዘቶች – ሲጨመቁ
- “የአማራ ክልል ሚሊሻዎች ትጥቅ ይፍቱ በሚል የሚሰራጩ መረጃዎች ‘ባልበላውም ጭሬ ላፍሰው’ ከሚል ቅዠት የተወለደ ቅጥፈት ነው”“የሚሊሻ ኀይሉን በተመለከተ የሚዘዋወረው መረጃ ፍጹም መሠረተ ቢስ ነው” ሲሉ ኮሎኔል ግርማ ገሰሰ አስታወቁ። “ቅጥፈት ነው” ያሉትና በፕሬዚዳንቱ… Read more: “የአማራ ክልል ሚሊሻዎች ትጥቅ ይፍቱ በሚል የሚሰራጩ መረጃዎች ‘ባልበላውም ጭሬ ላፍሰው’ ከሚል ቅዠት የተወለደ ቅጥፈት ነው”