ግብጽ የህዳሴው ግድብ ከፍተኛ የውሃ እጥረት የሚያስከትል በመሆኑ አለምአቀፍ የሰላምና መረጋጋት ችግር መንስኤ ነው በማለት የጸጥታው ምክር ቤት አጀንዳ እንዲሆን ያቀረበችው ሀሳብ ተቀባይነት እንዳላገኘ ዘናሽናል ኒውስ ዘግቧል።
ግብጽ በተደጋጋሚ የህዳሴው ግድብ በሀገሪቱ ብሔራዊ ጥቅም ላይ አደጋ እንደደቀነባት ስሞታ ስታቀርብ ከመቆየቷም ባሻገር ግድቡን ለማፍረስ ወታደራዊ እርምጃን ጨምሮ ማንኛውንም አማራጭ እንደምትጠቀም መግለጿ የሚታወስ ነው።
በአንፃሩ ኢትዮጵያ ግድቡ በታችኞቹ ተፋሰስ ሀገራት ላይ ጉዳት እንደማያደርስ ብዙ ጊዜ አሳውቃለች። ግብጽ የጸጥታው ምክር ቤት የውሃ ጉዳይ አጀንዳው እንዲያደርግና የህዳሴው ግድብም ዓለም አቀፍ አጀንዳ እንዲሆን ጥያቄ ብታቀርብም ምክር ቤቱ ጉዳዩ የልማት አጀንዳ እንጂ የሰላምና ጸጥታ አለመሆኑን በማስገንዘብ ጥያቄውን ውድቅ አድርጓል።
ሀገሪቱ ባሳለፈነው አንድ ዓመት ብቻ በተደጋጋሚ ጉዳዩን ወደ ጸጥታው ምክር ቤት ለመውሰድ ከፍተኛ ግፊት ማድረጓ የሚታወስ ነው። የጸጥታው ምክር ቤት የግብጽን ጥያቄ ውድቅ በማድረግ ሶስቱ ሃገራት በአፍሪካ ህብረት መሪነት ገንቢና ትብብር በተሞላበት መንገድ በአፋጣኝ ወደ ድርድሩ እንዲመለሱ አሳሰቧል።
በተባበሩት መንግስታት የኢትዮጵያ አምባሳደር ታዬ አጽቀስላሴ ምክር ቤቱ አለምአቀፍ ሰላምና መረጋጋትን የተመለከቱ ጉዳዮችን ብቻ የማየት ስልጣን እንዳለው በመጥቀስ፤ ጉዳዩ የሚቋጨው በሶስትዮሽ ድርድር ብቻ በመሆኑ ግብጽና ሱዳን ወደ ድርድሩ ፈጥነው እንዲመለሱ መጠየቃቸውንም ናሽናል ኒውስን ጠቅሶ ኢዜአ አመልክቷል።
- National Dialogue, Transitional Justice And Rehabilitation Process Pillars of Lasting Peace, Prosperity: CouncilThe Ethiopian National Security Council has issued a statement on latest developments in the country. In its statement, the… Read more: National Dialogue, Transitional Justice And Rehabilitation Process Pillars of Lasting Peace, Prosperity: Council
- Somaliland offended by G7 referring the Republic of Somaliland as “Somaliland Region of Somalia” The Republic of Somaliland, is a sovereign state with its own laws and constitution, reaffirmed by the people of… Read more: Somaliland offended by G7 referring the Republic of Somaliland as “Somaliland Region of Somalia”
- Foreign firms’ local market involvement entails economic dynamismPermitting foreign firm’s involvement in the import, wholesale and retail business, which was restricted to local companies, would bring… Read more: Foreign firms’ local market involvement entails economic dynamism