በወለጋ የተለያዩ ግንባሮች የኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች መሪ ናቸው የተባሉትን ጨምሮ ለጊዜው ቁጥራቸው ይፋ ያልሆነ ታጣቂዎች መማረካቸው ተሰማ። በመተከል ዞን ማንዱራ ወረዳ ታጥቀው ሲንቀሳቀሱ የነበሩ የጉህዴን ታጣቂዎች የመንግሥትን የሰላም ጥሪ ተቀብለው መመለሳቸውን ተቤኒሻንጉል ክልል ኮሙኒኬሽን ጽህፈት ቤት ምስልና ቪዲዮ አስደግፎ አስታወቀ።
በዳሬ ሰላም የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት አመራሮች ጋር ንግግር እየተደረገ ባለበት በአሁኑ ሰዓት ኦፕሬሽኑ ተጠናክሮ መቀጠሉን ያስታወቁት ክፍሎሽ እንዳሉት በሰሙሉ ወጊያ በተለይም ከትናንት በስቲያ የኦነግ ሸኔ አዋጊዎች ናቸው የተባሉ መማረካቸውን ተናግረዋል።
በአማራ ክልል የትጥቅ ትግል በሚያደርጉት የተለያዩ ስያሜ ያላቸው ላይ ታቂዎች ላይ በተመሳሳይ ሙሉ ማጥቃትና ማጽዳት መጀመሩ ይፋ በተነገረበት ወቅት፣ የኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች ሰፊ ይዞታቸውን እያጡና እየተማረኩ መሆናቸው መንግስት በይፋ ባይገልጽም በአካባቢው ያሉ ምስክሮች አረጋግጠዋል።
“በመተከል ዞን ማንዱራ ወረዳ በጫካ ውስጥ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ የጉህዴን ታጠቂዎች የመንግስትን የሰላም ጥሪ በመቀበል ወደ ሰላም ተመልሰዋል” ሲል ነው ቢሮው ይፋ ያደረገው።
በመኩሪያው ዚፋሃ እና በመኮነን ፋኖ በሚባሉ ግለሰቦች ሲመራ የነበረው የጉህዴን ታጣቂዎች ቡድን በውይይት የሰላም ስምምነት መቀበሉ ታውቋል። ውይይቱ ሰፊና ከፍተኛ ጥረት የተደረገበት እንደሆነ ተመልክቷል።
በማንዱራ ወረዳ ታጣቂዎች የሰላምን አማራጭ ተቀብለው ሲገቡ የዞኑ ከፍተኛ አመራሮችና የሀገር ሽማግሌዎች በገነተ ማሪያም ከተማ በመገኝት አቀባበል አድርገውላቸዋል።
የመተከል ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ለሜሳ ዋውያ፣ ታጣቂዎች የሰላም አማራጭ በመቀበል ወደ ህብረተሰቡ መመለሳቸው የቀጠናውን ሰላም በዘላቂነት የተረጋጋ እንዲሆን ያደርገዋል ብለዋል።
ተመላሾችን በተማሩበትና ፍላጎታቸውን ግምት ውስጥ በማስገባት በተለያዩ የግብርና ዘርፎች ለማሰማራት እንደሚሠራም ተናግረዋል።
በመተከል ዞን ማንዱራ ወረዳ ጫካ ውስጥ መቀመጫቸውን አድርገው በአዋሳኝ አካባቢዎች ስጋት ሲፈጥሩ የነበሩ ታጣቂዎች በውይይት መምጣቸው ለህብረተሰቡ ሰላም ዘላቂ መፍትሄ እንደሚሰጥም ነው የተገለጸው።
የሰላም ስምምነቱን ተግባረዊ ለማድረግና ወደ ሰላምና ልማት ለመግባት የሀገር ሽማግሌዎችና አመራሮች በተገኙበት ከሰላም ተመላሾች ጋር በጉሙዝ ብሄረሰብ ባህል መሠረት የእርቅ ስነ ስርዓት መካሄዱን የመተከል ዞን ኮሙኒኬሽን መምሪያ መረጃ ያመለክታል።
- Ethiopia Working To Secure New Development Bank MembershipThe Ministry of Foreign Affairs disclosed that Ethiopia is working hard to become member of BRICS’ New Development Bank. In a media briefing regarding the country’s diplomatic activities over the week, Spokesperson of the Ministry Nebiyu Tedla, indicated that Ethiopian delegation led by State Minister of Foreign Affairs Ambassador Mesganu Arga participated in the consultation… Read more: Ethiopia Working To Secure New Development Bank Membership
- የትግራይ ክልል ታጣቂዎች ዳግም ዝርፊያ እያፈጸሙ ነው፤ የተማሪዎች መጽሃትን “የአማራ ክልል ናቸው እየሉ ቀደዋል”በአላማጣ ከተማ በተለየ መልኩ የትግራይ ክልል ታጣቂዎች በከተማዋ ውስጥ እንደሚንቀሳቀሱ ነዋሪዎች መመስከራቸውን ቢቢሲ አስታወቀ። ይህ የተገለጸው ከአለማጣ እና አካባቢው የተፈናቀሉ ሰዎች ቁጥር ከሃምሳ ሺህ በላይ ማሻቀቡ ይፋ እየሆነ ባለበት ወቅት ነው። መንግስት ሰላማዊ ዜጎችን ማህበራዊ ዕረፍት መንሳት አግባብ እንዳልሆነ ጠቅሶ ” መንግስታዊ ሃላፊነትን መወጣት ፍርሃት አይደለም” ቢልም የትግራይ አመራሮች ሂደቱ ከመንግስት ጋር በተደረገ ስምምነት እየተከናወነ… Read more: የትግራይ ክልል ታጣቂዎች ዳግም ዝርፊያ እያፈጸሙ ነው፤ የተማሪዎች መጽሃትን “የአማራ ክልል ናቸው እየሉ ቀደዋል”
- በዘንድሮው ዓመት የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ኢትዮጵያ ሰባት ነጥብ ሁለት ቢሊዮን ችግኝ ልትተክል ነውለዘንድሮ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር 6 ነጥብ 5 ቢሊየን ችግኝ ለመትከል ዕቅድ መያዙንna ለዚህም ተግባራዊነት ከሰባት ነጥብ ሁለት ቢሊየን በላይ ችግኝ መዘጋጀቱን ተገለጸ። 1 ነጥብ 2 ሚሊየን ሄክታር መሬት ለተከላ ተዘጋጅቷል። More stories G7, IMF, NATO & et al- WOLF IN SHEEP’S CLOTHINGJune 15, 2021 ህወሓት ከሽብርተኛነት ተሰረዘMarch 22, 2023 ለአማራ ክልል በህቡዕ 450 አመራሮች መመልመላቸው፣… Read more: በዘንድሮው ዓመት የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ኢትዮጵያ ሰባት ነጥብ ሁለት ቢሊዮን ችግኝ ልትተክል ነው
- አፍሪካ ህብረት ” የውጭ ምንዛሪ ሒሳቡን ወደ ሌላ ሀገር ሊያዘዋውር ነው” የሚለው ዜና ሃሰት መሆኑን ህብረቱ አረጋግጠአፍሪካ ህብረት የውጭ ምንዛሬ አካውንቱን ወደ ሌላ አገር እንደሚያዘዋውር ተጠቅሶ በህብረቱ ስም የወጣው ዜና ሃሰት፣ ሆን ተብሎ የተቀነባበረ መሆኑን መንግስት አስታወቀ። መረጃው ቀድሞውንም ዜናው “ሴራ” ነው በሚል አስተያየት ከሰጡ ወገኖች ጋር የሚስማማ ሆኗል። ቀሲስ በላይ መኮንን አፍሪካ ህብረት ቅጥር ግቢው ውስጥ በሚገኘው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቅርንጫፍ ነገሩ ሲነቃ ከተሰወሩ ግለሰቦች ጋር ተገኝተው በሃሰተኛ ሰነድ 6.5… Read more: አፍሪካ ህብረት ” የውጭ ምንዛሪ ሒሳቡን ወደ ሌላ ሀገር ሊያዘዋውር ነው” የሚለው ዜና ሃሰት መሆኑን ህብረቱ አረጋግጠ
- አፍሪቃ ህብረት ምን አሰጋውና “ገንዘቤን ወደ ሌላ አገር ለማዛወር እያሰብኩ ነው” ሲል ተንሿከከ፤ የጾምና የፍስክ ዜናዎችባንኩ የክፍያ ሰነድ ቀረበለት። ማጣሪያ ጥያቄ ለህብረቱ አቀረበ። ሃሰት ሆኖ ተገኘና ፖሊስ ተጠርጣሪዎቹን ያዘ። ጉዳዩ ወደ ህግ አመራ። አሁን ምኑ ነው አፍሪካ ህብረትን ስጋት ላይ ጥሎት አካውንቱን ወደ ሌላ አገር እንዲወስድ ያስገደደው? ከሆነም ህብረቱ ይህን አቋሙን ለምን በይፋ ከማስታወቅ ይታቀባል? ነገሩ በዚህ ደረጃ አሳሳቢ ከሆነ ቢያንስ ሁለት መስመር መግለጫ እንዴት ማውጣት ተሳነው …. ብዙ መወያያ… Read more: አፍሪቃ ህብረት ምን አሰጋውና “ገንዘቤን ወደ ሌላ አገር ለማዛወር እያሰብኩ ነው” ሲል ተንሿከከ፤ የጾምና የፍስክ ዜናዎች