ኡ ኡ ኡ ኡ …. ለሚሰማ፤ ሰሚ ካለ … ኡ ኡ ኡ ኡ መንግስትን ውቀጠው። ቀጥቅጠው። ዘልዝለው። ባለስልጣኑንን ማንም ይሁን ማን አትልቀቀው። መተንፈስ እስኪያቅተው አበራየው፣ አንገዋልና ለነፋስ ስተው። ስራው ያውጣው። መረጃ!! ተጨባጭ የሆነ መረጃ፤ የሚናደፍ ምላስ ሳይሆ መረጃ ግድ ነው። ይህ ሳይሟል ከመጸዳጃ ቤት፣ ከሰገራ ቤት መረጃ ማጣቀስ ቅዳቂነት ነው። የሽንት ቤት መረጃን ፈጽሞ አታጣቅስ። የሽንት ቤት ግድግዳ ላይ ጽሁፎች መረጃ ሆነው አያውቁም። የመጸዳጃ ቤት ጽሁፎች አጣቅሶ መንግስትንና ሃላፊዎችን ማራከስ አይነፋም። ቧልት ነው። የጎ ፈንድ ገበያ ነዳጅ ነው። የዲጂታል አቁማዶ / መለመኛ ነው። ውሎ አድሮ ያዋርዳል። ያሳፍራል። የልጅ ልጅ ያፍርበታል። የልጅ ልጅ የሚወርሰው ጠባሳ ይሆናል። ያበደው እንቅጭሁን ይናገራል።
- ስቶኮልም ሲንድረም … ያሰቃየህን የመናፈቅና የማፍቀር፣ እንዲሁም አዳኝ አድርጎ የማሰብና የማመን በሽታ ነው። ወደ ኢትዮጵያ ሲመለስ “በሬ ያኮላሸውን” እንደማለት ነው። በሬው ጨው መላሱን እንጂ ቂጡና ማጅራቱ አብጦ ለእርድ እንዲሆን ጨው አልሰው ብልቱን እመቀመጫው ድረስ እንደቀጠቀጡት አይገባውም። የቦሰና ረቂቅ እይታ ነው። ጨውና በሬ!!
“ቦሰና ቤተሰብ፣ ሚስት፣ ልጆች፣ ዘመድ፣ አዝማድ፣ ወዳጅ፣ ፈርሃ ፈጣሪ ያላቸው” ትልና ጣልቃ ገብተው ለማረቅ ለምን እንደማይሞክሩ ስታስብ ትነግፈገፋለች። ሰው አፈናቅሎ፣ አጋድሎ፣ አገር ላይ መርዝ እየረጩ በሚሰበስቡት ገንዘብ የምታጌጪ ሚስት፣ ልጆች፣ ይህንኑ የዕርም፣ የዕንባና የብዙሃን ስቃይ ድምር ሃብት እየሰበሰባችሁ ልጆቻችሁን የመትመግቡ ዋ!! ዋ!! ዋ!! ትግራይ፣ አማራ፣ ሃዋሳ፣ ኦሮሚያ፣ ሶማሊሌ፣ ቤኒሻንጉል … እናቶች፣ አቅመ ዳካሞች፣ አዛውንቶች፣ እመጫቶች፣ በጫካ የተወለዱ ህጻናት ሲቃ ወደ ሰማይ ይጮሃል … ጫካ ውስጥ የዛፍ ስር ይዛ አምጣ የተገላገለች ወይም የቀበረች የምጧ ስቃይና ሃዘኗ እላይ ይጮሃል…. ያበደው አነባ። ምን ያለ ጭካኔ … ምን እንሁን? ምን እስኪሆን ይሆን በማተራመስ፣ አተራምሶ ኪስ በመሙላት የሚዘለቀው? ይህም እንደ ኩራት ” አይበገሬው፣ አንበሳው፣ ትንታጉ …” እያሰኘ …. የሚዘፈነው፤ ለዚህ ክፋት በሰልፍ ግብር በኦንላይን የሚገባለት? ያበደው ተወራጨ። ህዝብ አዳም የመርዝ አካእፋፋዮችን ” ሰርተህ ብላ” እንዳይል፣ “ከጌቶቻቹህ” ተቀበሉ ሲል አበሻቅጦና አራክሶ ከማባረር ይልቅ ” በጎ ፈንድ” ይመዘገባል። በሱፐር ቻት ስሙ ሲጠራ፣ ስሟ ሲነሳ እየወበቀው፣ እየወበቃት ደም ተፍታ የሰብሰበችውን ታስረክባለች። አያስረክባል። በዘምናዊ ለማኞች መደንዘዝ!!
በማያውቁት፣ በሌሉበት የታረዱ፣ የተሰቀሉ፣ ስቅላት በቂ ስላልነበር ተሰቅለው የድንጋይ ወገራ የተመረቀላቸው፣ ይህ ሲሆን ፊልም እየቀረጹ መዋጮ የሚሰበስቡ፣ እምባቸው ወደ ላይ ፈሷል። ቤታቸው እያነደድክ ስትገልፍጥ የነበርክ ግፍህ ሰማይ ነክቷል። እንዲህ ያለውን ቪዲዮ የምታሰራጭና ተጨማሪ ደም ለመጋት ሴራ ስትጎነጉን የነበርክ ሁሉ የአጅህን አግኝተሃል ወይም ታገኛለህ። ማንም ሁን ማን የስማዩ አባት ያውቅሃል። በቤትህ እንደ በለአም መዓት ይወርድብሃል። እንዳሴርክ አትኖርም። ባለ ጊዜም ሁን ተሰናባች ሁልህም ትሰፈራለህ። በሁሉም አቅጣጫ ደም የምትራጩ ይብቃችሁ። ስላበጣችሁና በልመና ስላሽከረከራችሁ … ያበደው ተናናቀው!! አተራማሾቹ ሊያተራምሱ ስቱዲዮ ከመግባታቸው በፊት ክትፎ ሲበሉ የተራገመቸው ሴት ፊቱ መጣችበት። ” ደም ብሉ፣ አፈር ብሉ” እያለች ተራግማለች። እመቤቴ ብላ እዛ እያፋረሱ እዚህ ራሳቸውን ሲገነቡ ለምን በዝምታ እንደምታይ ወቅሳለች። እነሱን ይሰለቅጡ ነበር። ያንቃርሩ ነበር። ለካ ለንግግር ያመች ዘንድ “ያስተፈስህ” ይወሰዳል!!! ያበደው ዞረበት።
… ሁሉም አንባቢና አነብናቢ ስለሆነ ጩኸቱ አሳክሯል። ከሁሉም ወገን የሚተፋው አንድ ላይ ሆኖ ለማድመጥ አይመችም። ጃዋር ገብቶት ይሁን ለስልት “ስለፈልፍ ስለኖርኩ ላድምጥ እስኪ ብዬ ዝም አልኩ አለ” ግን መናገር ጀመረ። ይህ ድምጽ ጤነነቱ ባይረጋገጥም በሁካታና ጩኸቱ መካከል ተሰምቷል። ኮሮጆ ጎድሏል መሰል የአውሮፓ ቱር እቅድ ወጥቷል። ለጊዜው ኦሮሚያ በትራክተር እያረሰ ነው። አማራም ከጥይት ጩኸት ወደ ትራክተር እየዞረ ነው። ኢትዮጵያን አንድ የህብረትሰብ ጤና ዶክተር እንዳሸነፏትና የታላላቅ ሰው ወዳጅ መሆናቸው ሲራገብ ነበር። አሳቡ “የጀግኖቹን መንደር” ለመቀላቀል የሚደረግ ርብርብ ይመስላል!! “የጀግኖቹ መንደር!!” አብዮታዊት ትህነግ ወይም ሞት በአደባባይ!! ታስሮ ጀግና መባልና እርጥባን መልቀም!!
ማታ ማታ አየሩ ይታጠናል። አማትበው የሚጀምሩ “እናትና ልጅ ይመስገኑ” ብለው የስድብ አረር ያጎርፋሉ። ከዛ ሲጨርሱ ” የደንቧን፣ የአገልግሎቴን እንዳትረሱ። ጣል ታል አድርጉ…” ይላሉ። ዲጂታል ለማኞች !! ያበደው ተቆጣ። የኔ ቢጤ እሜዳ ላይ፣ ጎዳና ላይ ቁጭ ብሎ ወይም አቁማዶ ይዞ ይለምናል። ራዳ የኔ ቢጤዎች በዲጂታል መስኮት ይለምናሉ። ቦሰና ” ኤዲያ ሁሉም ለማኞች ናቸው” ትላለች። እውነት ነው። ማታ ምታ ቁጭ ብለው ” ሰማሁ፣ ይመስለኛል” እያሉ የሚቀለቡ፣ ቀለቡ ሲጎድል ” አምጡ” የሚሉ ታዲያ ምን ሊባሉ ነው?
ያበደው ጩኸት ቢጠላም ከጩኸት ማምለጥ አልቻለም። ጩኸት ሰፈሩ ገበያ ነበር። የድሮው መርካቶ ያለው የተለመደው ” እዛው በላች እዛው ቀረች”ና የበርሜል ተራ አይነት ጩኸት አይደለም። ዲጂታል ጩኸት! በዘመነ መገናኛ ውስጥ ደንቁሮ መጮኽ … ደንቁሮ ማደንቆር… በኢትዮጵያ ባንዲራ እየተጠቀለሉ መጮህ!! እዛም፣ እዚህም፣ እወዲያም፣ እወዲህ፣ ማዶ ለማዶ መጮህ፣ መርጨት፣ መርዝ ማሰራጨት … መርዝ እየረጩ ” እርዱኝ” ማለት። እንደምን ከረማችሁ። ያበደው ከሰላምታው በፊት ቀባጠረ!! የሚረጨው ያስቀባጥራል። ሂሮሺማ!!
ግን ግን እውነቱ እንነጋገር ከተባለ እጅግ በጣም ጥቂት ከሚባሉ አገር ወዳዶች በቀር እነማን ናቸው ለሕዝብ ጥቅም ሲሉ የምርመራ ስራ ሰርተው የሚያቀርቡት? ስንት አስገራሚ የምርመራ “ጋዜጠኞችን” አወቅን? እንደው ምን አዲስ ነገር ነገሩን? በማስረጃ አስደግፈው ምን ያህል አገር የሚገነባ ቁስል አከሙ? “አብይ አባይን ሸጠው” ከሚለው የዛር ጩኸት ውጪ ምን ….. ያበደው በወጉ የሚሰሩትን ያከብራል። የፌስ ቡእክ ዜናን እየገለበጡ ሟርት የሚያደርጉትን ደግሞ ” ጊዜ የሰጠው ቅል .. ” ይላቸዋል።
የታክሲ ውስጥ ጽሁፍ፣ የግድግዳ ላይ ጽሁፍ፣ የሽንት ቤት ውስጥ ጽሁፍ አዎ የሽንት ቤት፣ የሰገራ ቤት ጽሁፍ ምንጩ ይታወቃል? ማን እንደቀባው የሚያውቅ አለ? እሽንት ቤት ውስጥ ቁጭ ብሎ የጻፈን ያየ ማን ነው? …. መልሱ!! ስሙንና መልኩን ደብቆ በየትኛውም አድራሻ የሚጽፍ ማን ነው? ማን ያውቀዋል? ለምን ይደበቃል? ምን ያስደብቀዋል? ይህ ከሰገራ ቤት ጽሁፍ በምንጭነት በምን ይለያል? ያበደው ይጠይቃል? ማንህ መልስ ያለህ? አሁንም ያበደው ይጠይቃል? መልስ የለም። ዝም ብሎ ተቀብሎ ማከፋፈል። መርጨት። አከፋፋዩን ” ትንታግ፣ የቁርጥ ቀን” እያሉ ማወደስ። ያበደው ” ደግነቱ ጥቂት ናችሁ። ኢትዮጵያ 130 ሚሊዮን ናት” ያለው እንቁራሪት ነጋዴ ታወሰው። አይ ቅኔ!! ፈገገ!!
ከፈርንሳይ ወደ ስድስት ኪሎ ከዛም ወደ ጃፓን ኤምባሲ ለማምራት እንደሶምሶማ እየሮጠ ” እኮ ነገረኝ” ይላል!! አዎ የሰገራ ቤት ጽሁፍ ምንጭ አድረገህ ለሌላ ታሰራጫለህ?” …. በለቤቱ ያልታወቀ ጽሁፍ፣ ቪዲዮ፣ አውዲዮ፣ ደብዳቤ … ከሰገራ ቤት የግድግዳ ጽሁፍ በመን ይለያል? መልስ የለም፤ ያበደው አሁን ጮክ አለ ቁልቁል ወደ ስድስት ኪሎ እየተምዘገዘገ …
“ታመና። ማላመጥ አቁመናል። ማየትና መመርመር ትተናል። ያገኘነውን ጥቅልል እየዋጥን ታንቀናል። መታነቃችን ጣር ሆኖብናል። ጣሩ ለሌሎችም በሚሰማ ደረጃ ስለሆነ ይረብሻል … አጣራ፣ መርመር፣ ዝም ብለህ አትዋጥ፣ አኝክ፣ አልም፣ ….” ያበደው ስድስት ኪሎ ደረሰ። ዘንዶ ልብ እንደገዙ መስማቱ አስታውሶ ” አርፋችሁ ተማሩ ብሎ ወደ አራት ኪሎ ሮጠ። አራት ኪሎ!!
አራት ኪሎ ለመግባት አቅደው የሚተጉ የሉም። ጥሩ አማራጭ ለመሆን የሚለፉ የሉም። ሁሉም አቋራጭ ፈላጊዎች ናቸው። አቋራጩ ደግሞ የትርምስ መንገድ ማበጀት ነው። ትርምሱ ደግሞ ፓኬጆች አሉት። ፓኬጅ አንድ፣ ሁለት፣ ሶስት፣ አራት … እያለ ይሄዳል። አስፈሳሚዎቹ የሚጮሁት ናቸው። ቦሰና እንዲህ ትላለች። “ሰው እንዴት ቀን በቀን በፈጠራ ሲሳደብ ይውላል”
በኢትዮጵያ የኩላሊት እጥበት ሆስፒታል ቢሰራ ዜና አይደለም። የተፈናቀሉ ቤታቸው ሲመለሱ ዜና አይደለም። ስንዴ ማምረት፣ ትራክተር ማደል፣ የደሃ ቤት መጠግን፣ ቆሻሻ መጥረግ፣ ችግኝ መትከል፣…. ውግዝ ነው። እንኳን ዜና ሊሆን ለርግማንም አይበቃም…. ያበደው “እቺ ተአምረኛ አገር” አለና ውጭ ጉዳይ ፊት ለፊት ቆመ። መናፈሻውን አየው። አብነት አትሮት ነበር። የተተናበረው የኢትዮጵያ ኢንዘስትመንት መንገድና የህዝብ መናፈሻ ይሸጥ ነበር። ተመስገን ዛሬ አርንጓዴ አምረፊያዎች እየተሰሩ ነው። ያበደው “ይቅርታ” አለ። በፈረሰ ልቡናቸው ግንባታ ስርስር እየሄዱ ” ሊያወድሙት ነው? ሊያጠፉት ነው? ሊሸጡት ነው …. የሚሉ ነቀዞችን አስታወሰ። አባይ ግድብ ስንቴ ተሽጦ፣ ስንቴ ፈርሶ፣ ስንቴ … “ምንጫችን ከውርልድ ባንክ ነገረን” ብለው አብይ አባይን መሸጡን የነገሩን እስካሁን ይቅርታ አልተየቁም። ዛሬም “ምንጫችን” እያሉ ነው …. አንተ ተከትልህ አራባ፡፤ አገርህ ላይ መርዝ እርጭ … ሳታስተውል በትነህ፣ ስትበተን ታርፈዋለህ ” እጄን በጄ …”
ማታ ማታ አየሩ ይታጠናል። አማትበው የሚጀምሩ “እናትና ልጅ ይመስገኑ” ብለው የስድብ አረር ያጎርፋሉ። ከዛ ሲጨርሱ ” የደንቧን፣ የአገልግሎቴን እንዳትረሱ። ጣል ታል አድርጉ…” ይላሉ። ዲጂታል ለማኞች !! ያበደው ተቆጣ። የኔ ቢጤ እሜዳ ላይ፣ ጎዳና ላይ ቁጭ ብሎ ወይም አቁማዶ ይዞ ይለምናል። ራዳ የኔ ቢጤዎች በዲጂታል መስኮት ይለምናሉ። ቦሰና ” ኤዲያ ሁሉም ለማኞች ናቸው” ትላለች። እውነት ነው። ማታ ምታ ቁጭ ብለው ” ሰማሁ፣ ይመስለኛል” እያሉ የሚቀለቡ፣ ቀለቡ ሲጎድል ” አምጡ” የሚሉ ታዲያ ምን ሊባሉ ነው?
የታክሲ ውስጥ ጽሁፍ፣ የግድግዳ ላይ ጽሁፍ፣ የሽንት ቤት ውስጥ ጽሁፍ አዎ የሽንት ቤት፣ የሰገራ ቤት ጽሁፍ ምንጩ ይታወቃል? ማን እንደቀባው የሚያውቅ አለ? እሽንት ቤት ውስጥ ቁጭ ብሎ የጻፈን ያየ ማን ነው? …. መልሱ!! ስሙንና መልኩን ደብቆ በየትኛውም አድራሻ የሚጽፍ ማን ነው? ማን ያውቀዋል? ለምን ይደበቃል? ምን ያስደብቀዋል? ይህ ከሰገራ ቤት ጽሁፍ በምንጭነት በምን ይለያል? ያበደው ይጠይቃል? ማንህ መልስ ያለህ? አሁንም ያበደው ይጠይቃል? መልስ የለም። ዝም ብሎ ተቀብሎ ማከፋፈል። መርጨት። አከፋፋዩን ” ትንታግ፣ የቁርጥ ቀን” እያሉ ማወደስ። ያበደው ” ደግነቱ ጥቂት ናችሁ። ኢትዮጵያ 130 ሚሊዮን ናት” ያለው እንቁራሪት ነጋዴ ታወሰው
በየመድረኩ ፈሱን ሲረጭ የነበረ “ጨዋ” ዛሬ ተንታኝ ነው። አዋቂ ነው። ዞሮ ዞሮ ሸቃይ ነው። ብቻ ሁሉም “ሱፐር ቻት” እያሉ ይቀፍላሉ። ተቀፋዮች ደም ተፍተው ከሚያገኙት ይሰጣሉ። ድርጎ ይሰፍራሉ … ሁሉም መርዙን እየረጨ ይለምናል። የማይለምኑ ጥቂት ናቸው። ሊለመናላቸው የሚገባቸው ብዙ አሉ። ግን ምርጫው “አተራምሰው፣ ነቃቅለው፣ ግፋ በለው፣ ቁረጠው፣ ድፋው፣ አፈናቅለው፣ አቃጥለው … ” የሚለው … ነው። ያበደው ከውጭ ጉዳይ ቁልቁል ተንደረደር። ለምን ወደ ጃፓን ኤምባሲ መሄድ እንደፈለገ አለገባውም። ግን እየሄደ ነው።
አሁን ምንጭ ማጣራት የፋራ ሆኗል። “ግፋ በለው” እርዳና ነው። ዘር ለይቶ የጅምላ ፍርድ መፍረድ አዋጪ ስራ ሆኗል። ሰሞኑንን ክፍት የስራ ማስታወቂያ ይወታል። የገቡትን ለመተካት የታሰበ ይመስላል። የብር ችግር የለም። መስፈርቱም ቀላል ነው። በጨበታ መነዳት ዋናው መስፈርት ሲሆን፣ ትንታጉ፣ አነጋጋሪው፣ አይበገሬው፣ ግንባሩ የማይታተፈው፣ የቁርጥ ቀን ልጅ፣ የታላቅነት ማማ፣ የጀግና ውሃ ልክ፣ የሞራል ጥግ፣ የክብራችን ምሶሶ፣ የኢትዮጵያ ወርቅ…” የሚሉትን ዝማሬዎች ያለ አፍረት መቀበል የሚችል። ከዚያ በተጨማሪ በሶስቱ ስላሴዎችና በአላህ የሚያምን። ያበደው ምራቁን ጢቅ አደረገ…. ኢትዮጵያን በወሬ፣ በፈተራ ሂሮሺማና ናጋሳኪ ማድረግ … በወሬ ኒኩለር ጢስ ማፈን … ያበደው ጃፓን ኤምባሲ ለመሄድ ያሰበበት ጉዳይ ታወሰው። ጃፓን አሁን ድረስ የመርዙ መዘዘ የታተመባቸው ልጆች እየታቀፈች ነው። ልብ ያባል!! ሌላ ቀን ወደ ኢምሬትስ ይሄድና ” እኔ በምሰራላችሁ ቤተ መንግስት ለምን ትርፍ ነገር ትናገራላችሁ። አሮጌዎቹ ቤተመንግስቶች ሙዜየም ሲሆኑ ከአፍሪካ አንደኛ ሙዜይም እንደሚሆኑና ከፍተኛ የገቢ ምንጭ እንደሚያስገኙ እንዴት ማስላት አቃታችሁ” ብለው እንዲላጡብን ማድረግ የያበደው ዕቅድ ነው። መሳይ መኮንን ምን አለ? ” አሁንስ ይህ መንግስት አበዛው” ድሮስ ? በሉና ጠይቁልን?
ስቶኮልም ሲንድረም … ያሰቃየህን የመናፈቅና የማፍቀር፣ እንዲሁም አዳኝ አድርጎ የማሰብና የማመን በሽታ ነው። ወደ ኢትዮጵያ ሲመለስ “በሬ ያኮላሸውን” እንደማለት ነው። በሬው ጨው መላሱን እንጂ ቂጡና ማጅራቱ አብጦ ለእርድ እንዲሆን ጨው አልሰው ብልቱን እመቀመጫው ድረስ እንደቀጠቀጡት አይገባውም። የቦሰና ረቂቅ እይታ ነው። ጨውና በሬ!! ቁራዎቹም እነደዚህ ናቸው። የልመናና የመቃተት ዘመናቸውን እንደ በሬው ዘንግተው ጨው ይልሳሉ። ይመኛሉ። ያንን ጨው !! ዲያስፖራ ሞኙ ሞኙ … ኪሱን ዘርግፎ ያበደው ሳቀ !! ምጽ!!
አሁን መሽቷል። ለአይን ያዝ እያደረገ ነው። ደጎልም በሃሳብ ያበደን ይናፍቃል። ደጎል ልዩ ውሻ ነው። ዩቲዩብ ላይ አማትበው ጀምረው የሚሳደቡትን፣ ኢየሱስ ብለው የሚነግዱትን ሲያይ ዘሎ ፊቱ ያዞራ። … ቦሰና እንደወትሮው ታጥናለች። ሙቀት ሲያምራት ቀድሞ ያናጫታል። ግን ከሰኮንዶች ነው። ማገዶ አትፈጅም። ወዲያው ክር፣ ወዲያው መርፌ ሲያሻትም ጂዶ ትችልበታለች። ቦሰና ስኳር ናት። ለቤቷም እመቤት ናት። ሙገሳ አትወድም። ሁሉም ነገር ለጋራ ጥቅም ሲባል እንደሆነ ታምናለች። ቦሰናና የግል ናት። ቤት ያላችሁ ግቡ። በቤታችሁ አግቡበት። የመጸዳጃ ቤት ጽሁፍ ለመረጃነት አይበቃም። ሰላም ሁኑ!!