አማራና አፋር ክልል በወረራ አመድ ሲሆን ትንፍሽ ያላሉት ዶክተር ቴዎድሮስ አድሃኖም፣ በአማራ ክልል በተከሰተው ግጭት መንገዶች መዘጋታቸው እንዲሁም የኢንተርኔት አገልግሎት እንዲቋረጥ መደረጉ የሰብዓዊ እርዳታን ማድረስ እና ግንኙነትን ለማስቀጠል ከባድ እንደሚያደርገው አመለከቱ። ሃዘናቸውን መግለጻቸው ደግ ቢሆንም በርካቶች ” የካድሬ ስብዕና ያስደንቃል” ሲሉ፣ ቀደም ሲሉ በነበራቸው የታጋይነት አቋም ሲዘልፏቸው የነበሩ ዜናቸውን እየተቀባበሉት ነው።
ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም በትዊተር ገጻቸው ይህን ያሉት በአማራ ክልል በታጣቂዎች እና በመንግሥት ጸጥታ አስከባሪዎች መካከል የተከሰተው ግጭት ተከትሎ ነው።
የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ግጭቶች በሰዎች ጤና ላይ በፍጥነት አሉታዊ ተጽእኖ ከማሳደራቸው በተጨማሪ በጤና ስርዓቱ ላይ ረዥም ጊዜ የሚዘልቅ ጉዳት ያስከትላሉ ብለዋል። ስጋታቸው ትክክል ቢሆንም ቴዎድሮስ ትህነግ አማራና አፋርን ወሮ ሲያወድም፣ ክሊኒክና ሆስፒታል ሲዘርፍና ሲያቃጥል ይህን አላሉም።
ዶ/ር ቴድሮስ ሰዎች የጤና ድጋፍ እንዳይቋረጥባቸው እና የዓለም ጤና ድርጅት ከአጋር ድርጅቶች ጋር በመሆን ሥራቸውን ማከናወን እንዲችሉ በክልሉ የጤና ስርዓቱ ጥበቃ እንዲደረግለት ጠይቀዋል። የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም “ከምንም በላይ ለሰላም ጥሪ እናቀርባለን” ማለታቸውን ቢቢሲ ነው የዘገበው። ትህነግ ተሸንፎ የሰላም ስምምነት ካደረግ በሁዋላ አደብ ገዝተው የተቀመጡት ቴዎድሮስ አድሃኖም አሁን ላይ የሰጡት መግለጫ ሳይሆን ቀደም ሲል ” እኔ ወያኔ ነ” እስከማለት ደርሰው ሲያስተላለፉ የነበሩት መረጃና አቋም ምን ግዜም ቢሆን ተዓማኝ እንደማያደርጋቸው ብዙዎች መግለጫውን ተከትሎ ገልጸዋል።
ባለፉት ሁለት ዓመታት በሰሜን ኢትዮጵያ ሲካሄድ የነበረው የእርስ በእርስ ጦርነት በአማራ ክልል ጨምሮ በጤና ስርዓቱ ላይ ከፍተኛ ጉዳት አስከትሎ እንደነበር የገለጸው ቢቢሲ ሃላፊ በወቅቱ በትህነግ አባልነታቸው ታውረው የአማራና አፋር ህዝብን ስቃይ በዝምታ ያልፉት እንደነበር አልተቆመም።
በመቶ ሺህዎች የሚቆጠሩ ተፈናቃዮችን በሚያስተናግደው ክልል የመድሃኒት እና የህክምና ቁሳ ቁስ ግብዓት እጥረት ከሰላም እጦት ጋር ተደማምሮ መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች እንቅስቃሴን ገድበው ቆይተዋል።
- የትግራይ ክልል ታጣቂዎች ዳግም ዝርፊያ እያፈጸሙ ነው፤ የተማሪዎች መጽሃፍትን “የአማራ ክልል ናቸው እየሉ ቀደዋል”በአላማጣ ከተማ በተለየ መልኩ የትግራይ ክልል ታጣቂዎች በከተማዋ ውስጥ እንደሚንቀሳቀሱ ነዋሪዎች መመስከራቸውን ቢቢሲ አስታወቀ። ይህ የተገለጸው ከአለማጣ… Read more: የትግራይ ክልል ታጣቂዎች ዳግም ዝርፊያ እያፈጸሙ ነው፤ የተማሪዎች መጽሃፍትን “የአማራ ክልል ናቸው እየሉ ቀደዋል”
- በዘንድሮው ዓመት የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ኢትዮጵያ ሰባት ነጥብ ሁለት ቢሊዮን ችግኝ ልትተክል ነውለዘንድሮ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር 6 ነጥብ 5 ቢሊየን ችግኝ ለመትከል ዕቅድ መያዙንna ለዚህም ተግባራዊነት ከሰባት ነጥብ ሁለት… Read more: በዘንድሮው ዓመት የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ኢትዮጵያ ሰባት ነጥብ ሁለት ቢሊዮን ችግኝ ልትተክል ነው
- አፍሪካ ህብረት ” የውጭ ምንዛሪ ሒሳቡን ወደ ሌላ ሀገር ሊያዘዋውር ነው” የሚለው ዜና ሃሰት መሆኑን አረጋግጠአፍሪካ ህብረት የውጭ ምንዛሬ አካውንቱን ወደ ሌላ አገር እንደሚያዘዋውር ተጠቅሶ በህብረቱ ስም የወጣው ዜና ሃሰት፣ ሆን ተብሎ… Read more: አፍሪካ ህብረት ” የውጭ ምንዛሪ ሒሳቡን ወደ ሌላ ሀገር ሊያዘዋውር ነው” የሚለው ዜና ሃሰት መሆኑን አረጋግጠ
- አፍሪቃ ህብረት ምን አሰጋውና “ገንዘቤን ወደ ሌላ አገር ለማዛወር እያሰብኩ ነው” ሲል ተንሿከከ፤ የጾምና የፍስክ ዜናዎችባንኩ የክፍያ ሰነድ ቀረበለት። ማጣሪያ ጥያቄ ለህብረቱ አቀረበ። ሃሰት ሆኖ ተገኘና ፖሊስ ተጠርጣሪዎቹን ያዘ። ጉዳዩ ወደ ህግ… Read more: አፍሪቃ ህብረት ምን አሰጋውና “ገንዘቤን ወደ ሌላ አገር ለማዛወር እያሰብኩ ነው” ሲል ተንሿከከ፤ የጾምና የፍስክ ዜናዎች
- የኢትዮጵያ ኤልክትሪክ ኃይል 300 ቢሊዮን ብር የንግድ ባንክ ዕዳ አለብኝ አለ፤ ዕዳውና የክፍያው ጫና እንደከበደውም አስታውቋልየኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከንግድ ባንክ 300 ቢሊዮን ብር ዕዳ እንዳለበት ተገለጸ። የዕዳ ጫናውን ለማቃለል የባንክ ወልዱም ጭምር… Read more: የኢትዮጵያ ኤልክትሪክ ኃይል 300 ቢሊዮን ብር የንግድ ባንክ ዕዳ አለብኝ አለ፤ ዕዳውና የክፍያው ጫና እንደከበደውም አስታውቋል