አማራና አፋር ክልል በወረራ አመድ ሲሆን ትንፍሽ ያላሉት ዶክተር ቴዎድሮስ አድሃኖም፣ በአማራ ክልል በተከሰተው ግጭት መንገዶች መዘጋታቸው እንዲሁም የኢንተርኔት አገልግሎት እንዲቋረጥ መደረጉ የሰብዓዊ እርዳታን ማድረስ እና ግንኙነትን ለማስቀጠል ከባድ እንደሚያደርገው አመለከቱ። ሃዘናቸውን መግለጻቸው ደግ ቢሆንም በርካቶች ” የካድሬ ስብዕና ያስደንቃል” ሲሉ፣ ቀደም ሲሉ በነበራቸው የታጋይነት አቋም ሲዘልፏቸው የነበሩ ዜናቸውን እየተቀባበሉት ነው።
ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም በትዊተር ገጻቸው ይህን ያሉት በአማራ ክልል በታጣቂዎች እና በመንግሥት ጸጥታ አስከባሪዎች መካከል የተከሰተው ግጭት ተከትሎ ነው።
የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ግጭቶች በሰዎች ጤና ላይ በፍጥነት አሉታዊ ተጽእኖ ከማሳደራቸው በተጨማሪ በጤና ስርዓቱ ላይ ረዥም ጊዜ የሚዘልቅ ጉዳት ያስከትላሉ ብለዋል። ስጋታቸው ትክክል ቢሆንም ቴዎድሮስ ትህነግ አማራና አፋርን ወሮ ሲያወድም፣ ክሊኒክና ሆስፒታል ሲዘርፍና ሲያቃጥል ይህን አላሉም።
ዶ/ር ቴድሮስ ሰዎች የጤና ድጋፍ እንዳይቋረጥባቸው እና የዓለም ጤና ድርጅት ከአጋር ድርጅቶች ጋር በመሆን ሥራቸውን ማከናወን እንዲችሉ በክልሉ የጤና ስርዓቱ ጥበቃ እንዲደረግለት ጠይቀዋል። የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም “ከምንም በላይ ለሰላም ጥሪ እናቀርባለን” ማለታቸውን ቢቢሲ ነው የዘገበው። ትህነግ ተሸንፎ የሰላም ስምምነት ካደረግ በሁዋላ አደብ ገዝተው የተቀመጡት ቴዎድሮስ አድሃኖም አሁን ላይ የሰጡት መግለጫ ሳይሆን ቀደም ሲል ” እኔ ወያኔ ነ” እስከማለት ደርሰው ሲያስተላለፉ የነበሩት መረጃና አቋም ምን ግዜም ቢሆን ተዓማኝ እንደማያደርጋቸው ብዙዎች መግለጫውን ተከትሎ ገልጸዋል።
ባለፉት ሁለት ዓመታት በሰሜን ኢትዮጵያ ሲካሄድ የነበረው የእርስ በእርስ ጦርነት በአማራ ክልል ጨምሮ በጤና ስርዓቱ ላይ ከፍተኛ ጉዳት አስከትሎ እንደነበር የገለጸው ቢቢሲ ሃላፊ በወቅቱ በትህነግ አባልነታቸው ታውረው የአማራና አፋር ህዝብን ስቃይ በዝምታ ያልፉት እንደነበር አልተቆመም።
በመቶ ሺህዎች የሚቆጠሩ ተፈናቃዮችን በሚያስተናግደው ክልል የመድሃኒት እና የህክምና ቁሳ ቁስ ግብዓት እጥረት ከሰላም እጦት ጋር ተደማምሮ መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች እንቅስቃሴን ገድበው ቆይተዋል።
- የበርሊን ማራቶን ባለማዕረግ ትግስት እነ ዱቤ ጂሎ ቢሳተፉ ታዝረከርካቸው ነበርበማራቶን ከሁለት ደቂቃ በላይ ማሻሻል እጅግ የሚደነቅና ያልተለመደ ነው። ባለሙያዎቹ ወይም አሰልጣኞቹ የሮጠችበትን ፍጥነት በሰዓትና ርቀት ከፋፍለው ቢያቀርቡት ምን አልባትም ወንዶችን የሚገዳደር ፍጥነት ተጠቅማ ሮጣለች። የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ተቴክኒክ ዳይሬክተርና የአትሌቶች ኮሚሽን ሰብሳቢ የነበሩት የዛሬው የተከበሩ ዱቤ ጅሎ አይነቱን ሯጮችን አዝረክርኮ ማሸነፍ የሚያስችላትን ሃይል አሳይታለች። የበርሊና ባለ ማዕረግ ትዕግስት!! ተግስት … Read moreContinue Reading
- ለወልቃይት ጠገዴ ሴቲት ሁመራ አንድ ሚሊዮን የጉልበት ሰራተኛ ይፈለጋል፤ ከአንድ ነጥን አንድ ሚሊዮን ኩንታል በላይ ሰሊጥ ይጠበቃል“ከየትኛውም የኢትዮጵያ ክልል አስተማማኝ ሰላም ያለው እዚህ ነው። ለሰራተኞች እንደ ቤተሰብ ዝግጅት አድርገናል። ኑ” ሲሉ የተሰሙት አምስት መቶና ሶስት መቶ ሄክታር ሰሊጥና ማሽላ ያመረቱ ባለሃብቶች ናቸው። የዞኑ ግብርና ቢሮ ሃላፊ እንዳሉት አንድ ሚሊዮን አንድ መቶ ሃምሳ ሁለት ሺህ ኩንታል የሰሊጥ ምርት ስለሚጠበቅ ከአንድ ሚሊዮን በላይ የሰራተኛ ሃይል ያስፈልጋል። የዞኑ አርባ … Read moreContinue Reading
- የጎንደርን ከተማ ምን አይነት ተኩስ እንደሌለ ተገለጸ፤ ጎንደር ተይዛለች ተብሎ ነበር“ጎንደር ከተማን ሙሉ በሙሉ ይዘናታል” ሲሉ ስማቸው እንዳይገለጽ ጠይቀው ለጀርመን ድምጽ መረጃ በሰጡ የአማራ ሕዝባዊ ኃይል ፋኖ ቃል አቀባይ አየር ማረፊያውን ሆን ብለው እንዳልያዙ አመልክተዋል። እሳቸው ተናገሩ የተባለው በጀርመን ድምጽ እየተሰማ በለበት ሰዓት በተመሳሳይ የጎንደር ከተማ አስተዳደር ውጊያ መደረጉን ሳያስተባብል ከተማዋን ለመያዝ የገባው ሃይል መደምሰሱን አሃዝ ጠቅሶ አመልክቷል። አገር መከላከያም … Read moreContinue Reading
- “የሞተው ባልሽ ገዳዩ ወንድምሽ፣ሀዘንሽ ቅጥ አጣ ከቤትሽ አልወጣ”የሞተው ባልሽ ገዳዩ ወንድምሽ (ሀዘንሽ ቅጥ አጣ ከቤትሽ አልወጣ) የሚለው የቆየ ተረት ልብን የሚያደማ ኩነትን ማሳያ ነው። እቺ መከረኛ ሚስት ባልዋ በእናቷ ልጅ ወንድሟ ተገደለ። ሟች ባል፣ ገዳይ ወንድም … ኢህአፓ “ሃይማኖት ነው” በሚል ሲገልጸው በነበረው ትግል በቀይና ነጭ ሽብር ስም እናቶች የወላድ መካን ሆነዋል። ጧሪ ያጡና ባዶ ቤት ሃዘን … Read moreContinue Reading
- በአማራ ክልል የተነሳው ጦርነት በሰላም ሊቆጭ እንደሚችል ተሰማበአማራ ክልል የተቀሰቀሰው ጦርነት በሰላማዊ መንገድ የሚቋጭበት አግባብ ተስፋ ሰጪ ደረጃ መድረሱ ተሰማ። የኢትዮ12 የዜና አቀባዮች እንዳሉት ሰላም ወደድ የሆኑ ዜጎች ችግሩን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት እያደረጉ ያለው ጥረት ውጤታም እየሆነ መሆኑንን ነው ያመለከቱት። በሰላም ጥረቱ ውስጥ የሚሳተፉትን ወገኖችና የሰላም ንግግር አመቻች የሆኑትን ክፍሎች ሳይጠቅሱ የዜናው ሰዎች እንዳሉት ጥረቱ ብዙ መንገድ … Read moreContinue Reading